በቻይና በተካሄደ አገር አቋራጭ የተራራ (አልትራማራቶን) ውድድር ላይ በተከሰተ ከባድ የአየር ሁኔታ የ21 ሯጮች ሕይወት አልፏል። በ100 ኪ.ሜ (60 ማይልስ) የአልትራማራ ውድድሩ በጋንሱ አውራጃ የቱሪስት ስፍራ በሆነው በቢጫ ወንዝ የድንጋይ ደን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መካሄዱ ተገልጿል።
በወቅቱም በተከሰተው ከፍተኛ ንፋስ እና በረዶ የቀላቀለበት ዝናብ አትሌቶቹ በመመታታቸው በውድድሩ ከተሳፉ 172 ሯጮች መካከል አንዳንዶቹ ሲጠፉ ÷21 ሯጮች ለህልፈት መዳረጋቸው ተገልጿል። ውድድሩ ተቋርጦም የነፍስ አድን ሥራ መጀመሩ ተመላክቷል።
በዚህም ከተሳታፊ አትሌቶች መካከል 151 የሚሆኑት ደህንነታቸው የተረጋገጠ ሲሆን÷ ከነዚህ ውስጥ ስምንቱ መቁሰላቸውም ነው ባለሥልጣናቱ የገለጹት ፡፡ ውድድሩ ሲጀመርም የተወሰኑ ተወዳዳሪዎችን ቁምጣ እና ቲሸርት ብቻ ለብሰው እንደነበር ነው የተገለጸው ፡፡
በሕይወት የተረፉት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየትም ÷የአየር ሁኔታው በእይታቸው ላይ ተጽዕኞ በማሳረፉ መንገዳቸውን መሳታቸውን ገልጸዋል። የአየር ንብረት ትንበያው የተወሰነ ንፋስ እና ዝናብ እንደሚጠበቅ ቢተነብይም እነሱ የገጠማቸውን ያህል የከፋ የአየር ጸባይ ሊኖር እንደሚችል አለመግለጹን ተናግረዋል።
ሩጫው ከተጀመረ ከሦስት ሰዓት ያህል በኋላ በተራራማው ክፍል በበረዶ ፣ በከባድ ዝናብ በመምታቱ የአካባቢው ሙቀት መጠኑን እንዲያሽቆለቁል ምክንያት መሆኑን በአቅራቢያው የሚገኘው የቤይን ከተማ ባለሥልጣናት ገልጸዋል ፡፡
የነፍስ አድን ስራው ሌሊቱን ሙሉ እስከ እሁድ ጠዋት የቀጠለ ሲሆን÷ ተጨማሪ የሙቀት መጠን መቀነሱ ፍለጋውን ይበልጥ ከባድ እንዳደረገው የቻይናው የዜና አውታር ዘግቧል ፡፡
ምንጭ፡-ቢቢሲ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ