ጋሽ አሜሪካ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ኢትዮጵያን እንደ ሸክላ በእጇ የሰራቻት እስኪመስል የሃገርን ሉዓላዊነት በሰብአዊ መብት ጥሰት ሰበብ እና በእርዳታ ስም ድብቅ የተንኮል እጇን በማርዘም ስትገፋ፤
ስለ ሃገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የዓለም-ዓቀፉ ማህበረሰብ በውገና ድርሰት እና በተሳሳተ ሱዛናውያን መረጃ እና የውሸት ትርክት የተዛባ ግንዛቤ መያዝ (ከዚህ ረገድ የፐብሊሲቲ ስራውን ከመስራት አንፃር የሃገሪቱ ሚድያዎች እና በየሃገሩ ያሉ አምባሳደሮች ብልጫ እንደተወሰደባቸውና ክፍተታቸው ሰፊ መሆኑ ልብ ይለዋል)
የፓለቲካ ርዕዮትንና የሃገርን ጥቅም በደንብ ያልለዩት ዱዝ “አዋቂዎቻችን” ደግሞ በደስታ ፌሽታ ሲፍከነከኑና ከበሮ ሲደልቁ፤
የግብፅ ድንፋታን እና የጎረቤት ሱዳንን ጭራ መቁላት እንዲሁም የጦርነት ትንኮሳ ስትመለከት፤
ለያዥ ለገናዥ አስቸግራ የነበረችው ትህነግ ቅሪት አካሏ ዛሬም አፈር-ልሶ ለመነሳት ሲውተረተር፣ ሲደነፍና የግጭት መርዝ ርጭት ሲያደርግ ስታይ፤
ሃገራችን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ 6ኛውን ምርጫ ለማድረግ ደፋ ቀና ስትል፤
የህዳሴውን ግድብ ለመሙላት ብሎም ለመጨረስ የመጨረሻው ምዕራፍ መቃረቡን ስታይ፤
ሃገሪቱ በግሽበትና በኑሮ ውድነት ተወጥራ የዜጎች ህይወት ሲፈተን፤
ሃገርን በመምራት ሃገሪቱን በሁለንተናዊ የእድገት ጎዳና ወደፊት ለመውሰድ በሚደረገው የፓለቲካ አማራጭ ውድድር የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ከአቅም በታች ወርደው ጉንጭ አልፋ እና አንዳንዴም እንቶ-ፈንቶ የሆነ ውሃ የማያነሳ የወፈፌ እና የንቅል ሙሾ አውራጅ ዥልጥ የዕድርተኞች ፓርቲ ስብስብ (በጣት የሚቆጠሩ ጠንካራ የመከራከርያ ነጥብ እና በሃሳብ ልእልና የሚሟገቱትን አይመለከትም) ዲስኩር ስትሰማ፤
በተለያዩ ቦታዎች በዜጎች ላይ በተለይም በትግራይ ክልል የሰብአዊ እርዳታ ፈተና መሆንና የዜጎች ደህንነት አጣብቂኝ ውስጥ መውደቅ
አለማቀፍ የዲኘሎማስ ስራው እጅጉን ፈተና የበዛበት ትንቅንቅ ሲሆን፤
አለማቀፍ ሚድያዎች ሲኤንኤ, ቢቢሲ እና አልጀዚራ በተናበበ መልኩ የፈጣሪዎቻቸውን ህልም ለማሳካት የውገና ዘገባዎችን እና የጦርነት ድግስና የሰቆቃ ድምፅ ኦኬስትሬት ሲያደርጉ ስታይ፤
የምዕራባውያኑን ጥቅም እስካልነካ ድረስ በየትኛውም የሃገራችን ክፍል ተፈፅሞ የነበረና የሚፈፀም በደል አዓለም-ዓቀፍ ሚድያዎች በተለይም ሲኤንኤ, ቢቢሲ እና አልጀዚራ … ሌሎችም ብዙም እንደማያስጨንቃቸው በተደጋጋሚ ስታይ፤
ከጊዜ ወደጊዜ የሃገሪቱ የፓለቲካ አካሄድ ውስብስብነት እየጨመረ መሄዱን፤
የማህበራዊ ሚድያው በአብዛኛው በሚባል ደረጃ መረን የለቀቀ የጦርነት ነጋሪት መጎሰሚያ እና የውሸት አውድማ መሆኑ … ወዘተ ስታይኢትዮጵያችን ምን አይነት ከባድ ሁለንተናዊ ፈተናዎች ምዕራፍ ላይ መሆኗን ታጤናለህ። ስለዚህ ዜጎች የፓለቲካ ጭምብላቸውን አውልቀው ነገሮችን ሁሉ በሃገራዊ ጥቅም መነፅር መመልከት ግድ የሚልበት ምዕራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ተገቢ ይሆናል።ሊነጋ ሲል ይጨልማል የሚባለው ብሂል ይሁን? ይነጋል!
በላይ ባይሳ
ግንቦት 20/2013 ዓ.ም
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the… Read more: The Wars We Still Can Stop