በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች በወዳጅነት አደባባይ በመገኘት የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለህዝብ ተወካዮች እና ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ከሚወዳደሩ እጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ትውውቅ ማድረጋቸው ተገለጸ።
በመርሐግብሩ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሀፍታይ ገብረ እግዚአብሄርን እና በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጅ የብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎችና አባላት ተገኝተዋል ።
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ብልጽግና ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ከዳር እስከ ዳር በማቀፍ በጋራ ሀገር የሚያስቀጥል ፓርቲ ነው ብለዋል ።
የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ኢትዮጵያን በመገንባት እና ዛሬ ላይ በማድረስ ትልቅ ሚና እንደነበረው ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።ከለውጡ በፊት በተለያየ መንገድ በተፈጠሩ ክፍተቶች የትግራይ ህዝብ በብዙ መልኩ ተጎጂ ነበር ያሉት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አሁንም የትግራይ ህዝብ ዳር ተመልካች እንዲሆን የሚሹ ሃይሎች አሉ፤ ያለንበት ምዕራፍ ግን እውነት ከሀሰት እየተለየ የሚወጣበት ወቅት ነው ብለዋል።ለሁሉም ነገር ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን የሚያደፈርስን ማንኛውም እንቅስቃሴ በጋራ መመከት እንደሚገባም ጠቁመዋል ሲል የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ዘግቧል።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል