በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚኖሩ ሁሉም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ምግብ የማግኘት የዜግነት መብታቸው እንዲጠበቅላቸው አስተዳደሩ ግዴታውን እንደሚወጣ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ተስፋ ብርሃን አራተኛው የምገባ ማዕከል ሥራ ጀመረ።
በልደታ ክፍለ ከተማ የተገነባው አራተኛው የተስፋ ብርሃን የምገባ ማእከል ትናንት በይፋ አገልግሎት መስጠት በጀመረበት መርሐ ግብር ላይ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች እንደገለጹት፤ ነዋሪዎች ምግብ ማግኘት የዜግነት መብታቸው ሲሆን፤ መንግሥትም ምግብ የማቅረብ ግዴታ ተጥሎበታል።
እነዚህ የምገባ ማእከላት እውን እንዲሆኑ በጎ አሳቢ ግለሰቦችና ተቋማት ትብብር ማድረጋቸውን የጠቆሙት ወይዘሮ አዳነች፤ ይህም በከተማው የሚስተዋለውን የማህበራዊ ችግሮች በአብሮነት በመተባበር ማቃለል እንደሚቻል ማሳያ ይሆናል። ችግሮቻችንን የምናቃልለው ስንተባበርና ስንተጋገዝ ነው ብለዋል።
ማዕከሉ በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር በቀን ከሁለት ሺ በላይ ተመጋቢዎችን ለመመገብ የሚያስችል አቅም እንዳለው ጠቁመው ፣ በማዕከሉ ተጠቃሚ የሚሆኑትም አካላዊና አዕምሯዊ ጉዳት ያለባቸው፣ በእጅጉ የኢኮኖሚ ውስንነት ያለባቸውና በገቢ እራሳቸውን ያልቻሉ ነዋሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ስላሴ ዋለልኝ፤ በልደታ ክፍለ ከተማ በተገነባው የምገባ ማዕከል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ህይወትን በመግፋት ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመደገፍና በምግብ እንዳይቸገሩ ለማድረግ የተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በክፍለ ከተሞች ብዛት ያላቸው የምገባ ማዕከሎች መገንባታቸው በየአካባቢው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚረዳ አመልክተው፣ በከተማው ውስጥ ከአካባቢ ወደ አካባቢ የሚደረገውን ፍልሰት ለመግታት እንደሚያግዝ አስታውቀዋል።
የማዕከሉ ተጠቃሚዎች ከምገባው በተጨማሪ የክህሎት ማሣደጊያ ፣ የሥራ ፈጠራ ስልጠና፣ የስነ ልቦና ምክር፣ እገዛና ህክምና እንደሚያገኙም ጠቁመዋል። ተጠቃሚ ዜጎች እነዚህን እድሎች ተጠቅመው የራሣቸውንና የሀገራቸውን እድገት ለማፋጠን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባቸው አመልክተዋል።
በማዕከሉ የምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ ተካ አስናቀ፣ ዜጋን ማሰብ ለሀገር ማሰብ ነው። አሁን ያገኘነው አገልግሎት አብሮ የመኖርን ትርጉም። መርሐ ግብሩ ምግብ ለማግኘት ጎዳና ወጥቶ የሀገር ገፅታን የሚያበላሽና በልመና የሚተዳደሩ አዛውንቶች፣ ህፃናትና ወጣቶችን ይታደጋል ብለዋል።
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የምንገኝ ዜጎች የእለት ጉርስ ከማሰብ ባለፈ ልማትና እድገትን፣ አንድነትንና የአገር ሰላምን እንድናስብ አድርጎናል። ተስፋ ሰንቀን የተሻለ ዜጋ ለመሆን እንድንጥር ባለሃብቶችና መንግስት ተባብረው ባደረጉት ተግባር ደስተኞች እንደሆኑ አስታውቀዋል።
ሙሳ ሙሀመድ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም