ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲደርስ ተጠርጣሪዋ ሰራተኛ እንደሌላት በመናገር ልትደብቃት ብትሞክርም ሰራተኛዋ ግን አልጋ ውስጥ ሆና ስትጮኽ ፖሊስ በመስማቱ ከስቃይ ሊያድናት እና አሰሪዋንም በቁጥጥር ስር ሊያውላት መቻሉን አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ የቤት ሰራተኛዋን በአሰቃቂ ሁኔታ ከ1 ዓመት በላይ ከቤት እንዳትወጣና የፀሃይ ብርሃን እንዳታገኝ በማድረግ፣ ምግብ በመከልከል ከፍተኛ ድብደባ ስትፈፅም የነበረች ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ተገለፀ።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ሲ.ኤም.ሲ አልታድ መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የሴቶችና ህፃናት ወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ኤርሚያስ ጋቸኖ እንደገለፁት አንዲት ግለሰብ በቤት ሰራተኝነት የቀጠረቻትን የ20 ዓመት ወጣት በተደጋጋሚ በመደብደብ፣ ምግብ በመከልከል፣ በር በመቆለፍ ከቤት እንዳትወጣ እና የፀሃይ ብርሃን እንዳታይ እያደረገች ስትበድላት ቆይታ የቤቱ አከራይ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት ይገኛል።
የግል ተበዳይ የሆነችው ወጣት ጥሩአለም ደጉ በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረች ጊዜ ጀምሮ ለ1 አመት ከ2 ወር ያህል ከባድ የሆነ ስቃይ ሲደርስባት እንደነበር በመግለፅ ፖሊስ ደርሶ ህይወቷን እንዲያተርፍላት ለቤቱ አከራይ በአጋጣሚ ባገኘችው የመስኮት ቀዳዳ ወረቀት ፅፋ መስጠቷን ተናግራለች ።
የቤቱ አከራይ አቶ ዮሐንስ ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው ሰራተኛዋን የተቀጠረች ቀን ብቻ ማየታቸውንና በተደጋጋሚ ያስቀጠራትን ደላላ ስለ ልጅቷ ጉዳይ መጠየቃቸውን ተናግረው በወረቀት ተፅፎ በመስኮት የተወረወረላቸውን መልዕክት ካገኙ በኋላ ለአቅራቢያቸው ፖሊስ ጣቢያ መጠቆማቸውን ገልፀዋል፡፡
ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲደርስ ተጠርጣሪዋ ሰራተኛ እንደሌላት በመናገር ልትደብቃት ብትሞክርም ሰራተኛዋ ግን አልጋ ውስጥ ሆና ስትጮኽ ፖሊስ በመስማቱ ከስቃይ ሊያድናት እና አሰሪዋንም በቁጥጥር ስር ሊያውላት መቻሉን አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ በአካባቢው የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶችን ለፀጥታ አካላት ሊጠቁምና በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል አካባቢውን በንቃት ሊመለከት እንደሚገባ ረዳት ኢንስፔክተር ኤርሚያስ ጋቸኖ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ዘገባ፡- ምክትል ሳጅን አዳነ ደስታ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and the ongoing tensions with Iran, its Foreign Minister Gideon Sa’ar found more time to visit Ethiopia. This visit underscores the importance of what the Israeli occupation minister discussed, and opens the… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን በቅጡ የሚገነዘቡ ምሁራን የራስ ዱሜራን ጉዳይ ወደ አደባባይ ይዘውት ቢመጡ እንዴት ጥሩ ነበር ምክንያቱም መልካም ሀሳቦች ሲጠራቀሙ ሀገር ያጸናልና! በጅቡቲ ላይ ወሳኝ ጥያቄ ማንሳት የሚያስችሉ ታሪካዊ አጋጣሚዎች የነበሩት ደርግ እና በኤርትራ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።ከትግራይ ጊዜያዊ መንበራቸው በአመጽና በጠመንጃ ኃይል እንዲወገዱ የተደረጉት አቶ ጌታቸው ውስን ያሉዋቸውን ጄነራሎች ስም እየጠቀሱና በጥቅሉ ተጋባራቸው “የብረሃን ስራ በብርሃን ነው” እንደተባሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ ስፔሻሊስት ስለነበርኩ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም ” – የራሱን ሰርግ አቋርጦ ቀዶ ሕክምና በማድረግ ሕይወት የታደገዉ ዶክተር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሌ ከተማ አስተዳደር የበሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ እያነጋገረ ነው። በቅርቡ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚንስትር ደኤታ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት በ “X” ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ቡድን ተቸካይ ነው። የትህነግ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ