በፌዴራል የጋራ ገቢዎች ቀመር መሠረት ባለፉት 11 ወራት ከ20.7 ቢሊዮን ብር በላይ የክልሎች ድርሻ መሆኑን በመለየት ማስተላለፍ መቻሉን የገቢዎች ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው ገለጹ።
ይህ የበጀት ክፍፍል ከአለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ 11 ወራት አንፃር ሲታይ የ16.6 ቢሊዮን ብር ወይም 400.14% ዕድገት አለው።ይህ ገንዘብ የክልሎችን የልማት ወጭ በመሸፈን ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው የገቢዎች ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው ገልጸዋል።
ለክልሎች የተላለፈው የገቢው ምንጭ ከኤክሳይዝ፣ ከተርን ኦቨር፣ ከተጨማሪ እሴት እና ከንግድ ስራ ገቢ ግብር ታክሶች ብቻ የተሰበሰበ ነው ተብሏል።የጋራ ገቢዎች ማከፋፈያ ቀመር በፌዴሬሽን ም/ቤት መሻሻል በመቻሉ፣ የተቋሙ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እያደገ በመምጣቱ እና ተቋሙ በተቀመጠው የማከፋፈያ ቀመር መሰረት ክፍፍሉን በአግባቡና በትክክል መስራት በመቻሉ የጋራ ገቢው ድርሻ ማደጉ ተገልጿል።
ክፍፍሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ታላቁና ፍትሃዊ ነው የተባለ መሆኑንን ለማሳየት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገላጭ መረጃዎችን ይፋ አድርጓል። በሰንጠረዥ አስደግፎ የቀረበው ማስረጃ ሃሜታንና የጎንዮሽ ወሬዎችን ያስቀራል ተብሏል።
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል
- ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂበኳታራውያን ባለሀብቶች የሚተዳደረው የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ያለውን ተደጋጋሚ የበላይነት በአውሮፓ ለማሳየት ከአሰልጣኞች አስከ ስመ ጥር… Read more: ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂ