\ስድስተኛውን አጠቃላይ አገራዊ ምርጫ የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ተገለጸ። የሕብረቱ የአጭር ጊዜ ታዛቢዎች ከምርጫው አንድ ሳምንት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ተገልጿል። በቅድመ ምርጫ ግምገማ የተሰማሩ ጉዟቸውን አጠናቀው ከምርጫ ቦርድ ጋር የመጨረሻ ውይይት ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበውን ግብዣ ተከትሎ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት ምርጫውን የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የአጭርና የረጅም ጊዜ ታዛቢዎችን ስምሪት ማድነቃቸው ይታወሳል።
ሕብረቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ ከሕብረቱ አባል አገራት የተውጣጡ ስምንት አባላት ያሉት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ግንቦት 25 እና 26 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ መግባቱን ገልጿል።
ታዛቢዎቹ በአጠቃላይ ምርጫ ሂደቱ ያለው የፖለቲካ ከባቢ አየር፣ የምርጫው ሕጋዊ ማዕቀፎች፣ የምርጫ ዝግጅትና አስተዳደር ግልጽነትና ውጤታማነት፣ የምርጫ ቅስቅሳ ሁኔታ የመታዘብ ስራ እንደሚያከናውኑም ተጠቅሷል።
ይህ በንዲህ እንዳለ ለቅድመ ምርጫ ግምገማ ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት ተቋማት ቅድመ ምልከታቸውን አጠናቀው ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ዛሬ ከምርጫ ቦርድ ጋር የሪፖርት ማሟያ ውይይት እንደሚያደርጉ ተሰምቷል። የኢትይ 12 የአዲስ አበባ ተባባሪ እንዳለው በቅድም ግምገማው ይህ ነው የሚባል የነቀፌታ ችግር እንዳልተገኘ ስራውን እየሰሩ ካሉ ሰምቷል።
አብዛኛው ሕዝብ ምርጫው ተደርጎ መገላገል እንደሚፈልግ፣ ከምርቻው በሁዋላ ሰፊ ተስፋ እንዳላቸውና የምርጫው መጠናቀቅ በጉልህ እንደሚያጠባበቁ የተሰበሰቡ አስተያየቶች እንደሚጠቁሙ የወሬው ምንጮች ገልጸዋል። በአንዳንድ ቦታዎች ረብሻ ይነሳል የሚል ስጋት ያላቸው ቢኖሩም ማን? ለምን? እንዴትና? የት ረብሻ እንደሚያደርግ አያውቁም። በወሬ ደረጃ ግን ሰዎችን የሚያስጨንቁ አሉ።
በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ዘንድ ስጋት እንደማይታይ ታዛቢዎቹ ተረድተዋል። አብዛኞቹ በተዘዋወሩባቸው ስፍራዎች ህዝብ የኮሮና ስጋት እንደሌለበት፤ ለስጋት የሚዳርግ ምንም ጉዳይ አለመኖሩን አይተዋል። ምርጫ ቦርድ ስጋት አለባቸውን ያላቸውን ስፍራዎች በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ምርጫ እንዳይካሄድባቸው መወሰኑ ይታወሳል።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ