በእንግሊዝ እየተካሄደ ያለው የቡድን 7 ሃገራት ስብስባ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል:: በመግለጫው የኢትዮጵያ ጉዳይም ተካቷል:: በአንቀፅ 54 ላይ የሰፈረው መግለጭ ቃል በቃል የሚከተለውን ይላል።

ትርጉም
54. “በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ባለው ግጭት እና እየወጡ ባሉ ሪፖርቶች ምናልባት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሁኔታ ውስጥ ሊሆኑ ስለሚችሉ የሰብአዊ አደጋዎች በጣም ያሳስበናል፡፡ የጾታ ጥቃትን ጨምሮ እየተፈፀሙ ያሉ አሰቃቂ ድርጊቶችን እናወግዛለን ፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን (OHCHR) ምርመራዎችንም በደስታ እንቀበላለን እንዲሁም በትግራይ ለተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሙሉ ተጠያቂነት እንዲሆኑና ወንጀለኞቹም ለህግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡ ግጭት በፍጥነት እንዲቆም ፣ ያልተዳረሰ ሰብዓዊ አቅርቦት ወደ ሁሉም አካባቢዎች እንዲደርስ እና የኤርትራ ኃይሎች በፍጥነት እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡ ለችግሩ ብቸኛ መፍትሄ ተአማኒ የፖለቲካ ሂደት ሁሉም ወገኖች እንዲከተሉ እንጠይቃለን፡፡ በቀጣይም የኢትዮጵያ መሪዎች የሰብአዊና የፖለቲካ መብቶችን በማክበር ላይ በመመስረት ብሄራዊ እርቅ እና መግባባት እንዲፈጠር ሰፋ ያለ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲያራምዱ ጥሪ እናቀርባለን፡፡” ትርጉሙ የተወሰደው ከደጀኔ አሰፋ ነው።
በዚህ አንቀጽ መሰረት ኢትዮጵያ ያልተስማማቸው ከትህነግ ጋር ንግግር የሚባለውን ህሳብ ነው። አልተካተተም። ጥቅል የፖለቲካ ፈውስ እንደሚያስፈልግ መንግስትም አምኗል። አስቀድሞ ተናግሯል። የሚገባ ምክር ነው ተብሏል። አሜሪካ ያወጣቸው መግለጫ ሲጨመቅ አይነት ነውልል
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ