ወ/ሪ ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመሩት የኢትጵያ ምርጫ ቦርድን ባልደራስ ክስ መስርቶ በክርከሩ ማሸነፉ ይታወሳል። ምርጫ ቦርድ የፍርድ ቤት ውሳኔን ባይነቅፍም ሕትመት በማጠናቀቁ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚቸገር መግለጡን ተከትሎ ያቀረበው የቴክኒክ ችግር የፍርድ ቤት ውሳኔን ወደ ጎን እንዳለ ተደርጎ ሰፊ ወቀሳ ሲሰነዘርበት እንደነበርም አይዘነጋም።
በመጨረሻም ምርጫ ቦርድ በሚሊዮን የሚቆጠር የህትመት ሰነዶች እንዲቃተሉ። እስክንድርና ሌሎች የባልደራስ አባላት የተካተቱበት የመረጮች ሰነድ እንዲዘጋጅ ከትናንት በስቲያ መውሰኑን ተከትሎ አዲስ መረጃ እየወጣ ነው። መረጃውም የተሰማው ከወደ ሂልተን አካባቢ ነው።
ለኢትዮ 12 የአዲስ አበባ ተባባሪ ትዝብቱን የሚያካፍለው የውጭ አገር ጋዜጠኛ እንዳለው ባልደራስ እነ እስክንድር ምርጫ የሚወዳደሩ ያልመሰላቸው ደጋፊዎቻችን ስላልተመዘገቡ ምርጫ ቦርድ ተጨማሪ የመመዝገቢያ ቀን እዲሰጣቸው ለመጠይቅ ማቀዳቸውን ትልቅ ለምትባለዋ አገር ዲፕሎማት ነግረዋል።
በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ10 ሰዓት እስከ ምሽቶ 9 ሰዓት ድረስ በአዘቦት ቀን የሃፒ ሰዓት ሂልተን በምርጫና በርዳታ የመጡ፣ እንዲሁም ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ የሆኑ የውጭ ዜጎች ይታደማሉ። የአገር ቤት አንዳንድ ሚዲያዎችና ፖለቲከኞችም እዛው መታየታቸው የተለመደ ሆኗል።
ባልደራስ አባላቱ እንዲመዘገቡለት ለዲፕሎማቱ ሲናገር የሰማው የሚዲያ ሰው እንዳለው ዲፕሎማቱ ስቀው ቀልድ ቢጤ ጣል አድርገዋል። ቀልዳቸው ውስጥ ” ምርጫውን አንሸነፋለን ብላችሁ ፈራችሁ እንዴ” ብለዋቸዋል።
ባልደራስ በተጣበበ ቀን የመራጭ ምዝገባ ቀን እንዲራዘምለት ማሰቡን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ተባባሪያችን የጠየቃቸው አንድ አባሉ ” የማውቀው ነገር የለም” ሲሉ ተቆጥተዋል። ስማቸውም ሆነ ማንነታቸው ከማናቸውም አስተያየታቸው ጋር እንዳይጠቀስ ተይቀዋል። ከሌሎች አመራሮች አስተያየት ለመስጠት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።
ኢትዮ 12 ባለፈው ሳምንት ምርጫው ሲቃረብ ራሳቸውን ለማግለል እየዶለቱ ያሉ ድርጅቶች መኖራቸውን፣ ፓርቲዎቹም በስም መለየታቸውንና የውጩ ማህበረሰብ ተወካዮችም ጠንቅቀው እንደሚያውቋቸው ቅድመ ምርጫ ዳሰሳ ላይ የሚሰሩ የአዲስ አበባ የምርጫ ታዛቢ መሪ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል።
ምርጫው ቀርቶ ሁሉም የተሳተፉበት የሽግግር መንግስት ይቋቋም የሚለውን አቋም በመናበብ የሚያራምዱ፣ የአሜሪካና የአውሮፓ መንግስታት፣ እንዲሁም ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ ፓርቲዎች በዚህ በተዥጎረጎረው አቋማቸው ወደ ምርጫው ቀን ተጠግተዋል።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza,… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም