የአገር መከላከያ ሰራዊት ለምርጫና ለሁለለተኛው የህዳሴ ግድብ ሙሌት እንከን እንዳይፈጠር በጥብቅ ዝግጅት ማድረጉ ተገለጸ። የምድርና የአየር ሃይል አዛዦች በተደጋጋሚ ይህንን ቢሉም ዛሬ በድጋሚ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ይህንኑ አጠንከረው አስታውቀዋል። በምርጫ ዙሪያ ወንጀል የሰሩም ተያዘዋል።
የመከላከያ ሚኒስቴርም ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት የተናገሩት ለአሐዱ ሬዲዮ ነው። 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የመከላከያ ሰራዊት ዝግጅት አድርጓል ነው ያሉት።
” በመላው ሀገሪቱ ወንጀለኛን አድኖ ለመያዝ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ ነው” ሲሉ ያስታወቁት ኮሎኔሉ በተለይ ስለተደረገው ዝግጅት ማብራሪያ አልሰጡም።
ኢትዮጵያ 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን መቁረጧ ይታወቃል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆኑ በየፊናቸው ከሚሰጡት መረጃ ለመረዳት ተችሏል። ብልጽግናም ስብሰባውን ሲያጠቃልል ምርጫው መሰላማዊ እንዲጠናቀቅ፣ ሁለተኛው የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ አቋም መያዛቸው ይታውሳል። ላለፉት አራት ወራት ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ የፖሊስ አባላት፣ በልዩ ልዩ ስልታዊ ተግባር የሰለጠኑ፣ ከፖሊስ ኮሌጅ የወጡ መኮንኖች በተከታታይ ሲመረቁ በክልል ደረጃም ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።
በለኢላ የምርጫ ዜና የምርጫ ቅስቀሳ ባነር ወይም የምርጫ ምልክት በመቅደድ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን በመያዝ እያጣራሁ ነዉ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን አስታወቋል።
ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ እየሰራሁ ነዉ ያለዉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የፖለቲካ ፓርቲዎች የቅስቀሳ ባነሮችን ቀደዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን መያዙን ገልፃል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፈንታ እንደተናገሩት በከተማዋ ስድስተኛዉን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የተሰቀሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባነርን በመቅደድ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን መያዙን ገልፀዉ ከነዚህ ዉስጥ በኮልፌ ቀራንዮ አንድ ግለሰብ የ5 ወር እስራት ተፈርዶበታል ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ኮማንደሩ አክለዉም የዘንድሮዉ ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ከዚህ በፊት ከተካሄዱ አምስት ሀገራዊ ምርጫዎች የተሻለ እና የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች በተሻለ የምርጫ ምልክታቸዉን በነፃነት እያስተዋወቁ ነዉ ሲሉ ጨምረዉ ገልፀዋል፡፡
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል