የያሬድ ጥበቡ ነገር
ብአዴን የተሰኘው ድርጅት በድን ሆኖ የኖረው ከአፈጣጠሩ ጀምሮ እንደ እስስት ተለዋዋጭ ባህሪ ባላቸው እንደ ያሬድ ጥበቡ( Yared Tibebu) አይነት ሰዎች በመመራቱ ይመስለኛል። አቶ ያሬድ ህወሓትን ከማምለኩ ውጪ በምንም ጉዳይ ላይ ጠንካራ አቋም ኖሮት አያውቅም። ዛሬ ያንቆለጳጰሰውን ነገ ተነስቶ ያለበቂ ምክንያት ሲቃወመው ታያለህ። ዝም ብሎ በነዱት ነው የሚነዳው።
(እንደ እኔ እንደ እኔ በየጊዜው አቋማቸውን የሚቀያይሩ ግልብ ሰዎች ሲያጋጥሙን እንደ ወንዝ ሳይሆን “እንደ ያሬድ ነው የሚነዱት” ብንል ሁላችንም ሊያግባባን የሚችል አገላለፅ ይሆናል ብየ አስባለሁ
ይህ ግለሰብ ከህወሓት አሽከርነቱ ተላቆ አሜሪካ መኖር ከጀመረ በርካታ አመታት ያስቆጠረ ቢሆንም አሁንም ድረስ ሞቶ የተቀበረውን ድርጅት ከማምለክ አልተመለሰም። በአንድ ወቅት “በረከት ስምኦን እና አዲሱ ለገሰ እንደ እንጀራ ይርቡኛል፤ እንደ ውሃ ይጠሙኛል” ብሎ ጉድ እንዳላስባለን አሁን ደግሞ ” ፃድቃን ገብረ ተንሳይ የአዲሱ የትግራይ ሰራዊት መሪ ሆኖ መምጣቱ በትግራይ ተስፋ እንዳልቆርጥ ያደርገኛል” ሲል እያስደመመን ይገኛል። ከወረዱ አይቀር እንደዚህ ነው።
ያሬድ እና መሰሎቹ ከሚፈፅሙት ድርጊት የተረዳሁት አንድ ነገር የወያኔ አሽከር ሆኖ ያገለገለ ግለሰብ በአካል ነፃ ቢወጣም አዕምሮው መቼም ቢሆን ከባርነት መላቀቅ የማይችል መሆኑን ነው። ለዚህም ይመስለኛል በመጦሪያ እድሜያቸው በረሃ የገቡት የቀድሞ ጌቶቹ ተአምር ይሰራሉ ብሎ ያመነው። አሁን እኮ አቶ ያሬድ የቀረው “መለስ ይመለሳል፤ ፃድቃን ያፀድቃል” ማለት ብቻ ነው
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ