በቅርቡ ከዳርፉር ግዳጃቸውን አጠናቀው የተመለሱትን የሰላም እስከባሪ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የትህነግ ቡድን በተለያየ ዓለም አቀፍ ተቋም ውስጥ በሚሠሩ የራሱ ሰዎች አማካይነት የተለያዩ ጫናዎችን በማሳደር ወደ ሀገራቸው እንዳይመለሱ ጥረት ማድረጉን የገለጹት የ25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል ተፈራ መላክ ናቸው፡፡
ኮሎኔል ተፈራ መላክ ጁንታው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሀሰት ወሬን እየነዛና ሠራዊቱ ውስጥ ባደራጃቸው ቅጥረኞቹ አማካይነት ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ ነበር ብለዋል፤ ለዚህ አንሸነፍም በማለት የሀገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ አንግበው የዘመቱት የሰላም አምባሳደሮች የጁንታውን ሴራ በማከሸፍ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡
የጁንታው ኃይል ኢትዮጵያ ሀገራችን በዓለም አቀፍ ሰላም የማስከበር ተልዕኮ ያላትን ስምና ዝና ለማጉደፍና ዝቅ ለማድረግ ቢጥርም በሠራዊቱ ጥንካሬ ይህ ሴራው ከሸፏል ያሉት ደግሞ የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምሕርት ቤት ዋና አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ ናቸው፡፡
አሸባሪው ሕወሃት ለትግራይ ሕዝብ አንዳችም የጠቀመው ነገር እንደሌለና አሁንም በሴራ የተተበተበ ስለመሆኑ ተግባሩ ይመሰክራል ያሉት የሠራዊቱ አባላት ይህን ኃይል የትግራይ ወጣቶች ሊታገሉት ይገባል ብለዋል፡፡ ምንጭ የመከላከያ ሚዲያ ዳይሬክቶሬት ነው
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል