በአዲስ አበባ ከተማ የጎዳና ተዳዳሪ በመምስል የሽብር ተግባር ለማስፈፀም የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ጨምሮ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ ከ900 በላይ ግለሰቦች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የተሰወኑት ግለሰቦች የጎዳና ተዳዳሪ በመምስል የሽብር ተግባር ለማስፈፀም ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም ተመክቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ የጎዳና ተዳዳሪ በመምስል የሽብር ተግባር ለማስፈፀም የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ለፀጥታ ስጋት የሆኑ ከ900 በላይ ግለሰቦችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጠቅሶ ኢዜአ ነው የዘገበው።
ኮሚሽኑ ከህዝብ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በጥናት ላይ በመመስረት በሰባት ክፍለ ከተሞች በተመረጡ 20 ቦታዎች ላይ ግንቦት 22 ቀን 2013 ዓ.ም ባከናወነው ኦፕሬሽን ቋሚ አድራሻ የሌላቸውና በዋና ዋና አደባባዮች እና በምሽት በሰዋራ ቦታዎች የተለያዩ ወንጀሎችን ሲፈፅሙ የነበሩ 999 ግለሰቦችን ይዞ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል አብዛኞቹ ማስቲሽና ቤንዚን በመጠቀም እራሳቸውን በማደንዘዝ የትራፊክ እንቅስቃሴዎችን ሲያውኩ እንደነበር በተለይ ደግሞ የትራፊክ መብራት ካስቆመው ተሽከርካሪ ላይ ስፖኪዮ ገንጥለው እንደሚወስዱ፣ ከአሽከርካሪ ወይም ከተሳፋሪ ላይ ሞባይል ስልክ፣ የአንገት ሃብል፣ ቦርሳ እና ልዩ ልዩ ንብረቶችን ቀምተው እንደሚሰወሩ ማረጋገጡን ገልጿል።
በተለይም ሴት አሽከርካሪዎች አደጋ ሳያደረሱባቸው አደጋ እንዳደረሱባቸው በማስመሰልና በማዋከብ ገንዘብ እንደሚቀበሉ፣ የትራፊክ አደጋ ሲያጋጥም ልዩ ልዩ ስልቶችን በመጠቀም ንብረቶችን እንደሚሰርቁ በጥቅሉ ትኩረታቸውን በዋና ዋና አደባባይ የትራፊክ መብራት በያዘው ተሽከርካሪ ላይ አድርገው ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበር ኮሚሽኑ ከህዝብ ከደረሰው ጥቆማና ባደረገው ጥናት ማረጋገጡን አመልክቷል።
ግለሰቦቹ በምሽት የቅሚያ ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበር መረጋጋጡ በተለይ ደግሞ የውጪ ሀገር ዜጎችንና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን በማዋከብና በማስጨነቅ በከተማዋ መልካም ገፅታ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ሲፈጥሩ እንደነበር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የተሰወኑት ግለሰቦች የጎዳና ተዳዳሪ በመምስል የሽብር ተግባር ለማስፈፀም ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ መገኘታቸውንም ኮሚሽኑ ገልጿል።
በከተማዋ የሚስታወሉ መሰል ስጋቶችን ለመቀነስ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረገው ህግን የማስከበር ተግባርና በተጠርጣሪዎቹ ላይ እየተደረገ ያለው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል፣ በወንጀል ተጠርጥረው ከተያዙት ግለሰቦች መካከል እንደ ድርጊታቸው መጠንና ስፋት በህግ የሚጠየቁት እንተጠበቀ ሆኖ እድሜያቸው አነስተኛና በወንጀል ድርጊት ተሳትፏቸው እጅግ ቀላል የሆኑት ደግሞ ከሚመለከተው የአስተዳደር አካል ጋር በመቀናጀት የተሃድሶ ስልጠና እንደሚሰጣቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ የከተማዋን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ተግባሩን አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ነዋሪው ለሰላም ስጋት የሆኑ ግለሰቦችን በመጠቆምና ማስረጃ በመሆን ተባባሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪ አቅርቧል፡፡
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም