በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።
ልጅ ግሩም ( ፒኤችዲ)
እርቅ፣ ሰላም እና ትብብር የሚል ሀሳብ ስለፈለገ ብቻ ነው። ግብፅን እንደ ምሳሌ እንመልከት፡-ግብፃውያን ከእስራኤል ጋር አራት ጊዜ ታላላቅ ጦርነቶችን አካሂደዋል፡፡ እስከ መጀመሪያው የግብፅ አብዮት መሪ ጋማል አብድል ናስር አስተዳደር ድረስ ከእስራኤል ጋር ሦስት ጦርነቶች ተካሂደዋል፡፡
ፕሬዝዳንት አንዋር ሳዳትንም አራተኛውን ጦርነት ተሸንፈው በኋላ ግን ፊታቸውን ወደ ሰላም አዞሩ፡፡ የዛሬ 40 ዓመት ገደማ በዘመኑ ብዙዎችን ያስገረመ ያስደነቀም ያልተጠበቀም ነገር አደረጉ፡፡ የሰላም እና እርቅ ንግግር ለማድረግ ወደ እስራኤል አቀኑ፡፡
ከዘመኑ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሜኒያሂም ቤጊን ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተው በመነጋገር የመጀመሪያው አረብ ሆኑ። በጊዜው ለፍልስጤማውያን ተቆርቋሪዎች ነን ይሉ የነበሩ የአረብ አገሮችና ሌሎች ሳዳትን በከሃዲነት አብጠለጠሏቸው፡፡
ሰላምን መምረጣቸው የተቀረውን ዓለም አድናቆት አተረፉ፣ ተወደሱ፣ ተሞገሱበት፡፡ እስራኤል በስድስቱ ቀን ጦርነት ከግብፅ የነጠቀችውንና በኋላም ያስፋፋችውን የሲናይ ግዛት ለግብፅ መለሰች። ፕሬዝዳንት ሳዳት የኖቤል የሰላም ሽልማት (1978) አሸናፊ ሆኑ፡፡ ከሶስት በኋላ ዓመታት በኋላ (October 6, 1981) በካይሮ በአንድ የሠልፍ ስነ-ስርዓት ላይ በህዝብ ፊት መድረክ ላይ ተቀምጠው እያሉ ተተኩሶባቸው ተገደሉ። በተመሳሳይ ስሌት ሰኔ 16 ቀን በመስቀል አደባባይ የተከሰተውን እናስታውሳለን።
በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።

- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ