አቶ ጌታቸው ረዳ ” ወደ ደብረብርሃን ወይስ ጎንደር” ሲሉ ወዳሻቸው የሽር ሽር ያህል እንደሚያቀኑ ባስታወቁ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ቆቦን መነተቃቸው ተሰማ። በአፋር ግንባር ከፈተኛ ቁጥር ያላቸው ምልምሎች መማረካቸው ታወቀ።

የአሸባሪው ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው እንዳሉት እሳቸው የሚወክሉት ጦር ወደ ፈለገው አቅጣጫ ለመሄድ የሚገድበው አንዳች ሃይል የለም። መደራደር እንደሚፈልጉ የሚነገርላቸው ጄነራል ጻድቃንም ” ወደ አዲስ አበባ ለመገስገስ የምያግድ አንዳችም ነገር የለም” የሚል ቃለ ምልልስ አድርገዋል።
ዛሬ ረፋዱ ላይ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለቱት ትህነግ ቆቦን ከሙሉ ኪሳራ ጋር ተነጥቋል። በአፋር ግንባር ሰፊ ቦታ የሚሸፍን ጦርነት ለመክፈት ሲያጋግዛቸው የነበሩ ምልምል ወታደሮች ከመኪና ሳይወርዱ ተይዘዋል። ከአካባቢው ምስክሮች መረዳት እንደተቻለው የተያዙት ከመኪና ሳይወርዱ በመሆኑ ” ተማረኩ” ሊባል አይችልም።
ከተማረኩት በተጨማሪ በሺህ የሚቆጠሩ መደምሰሳቸውን በስፍራው ያሉ ምስክሮች ገልጸዋል። የጅቡቲ ባቡርና የየብስ መንገድ እንደሚቆርጡ ከሳምንት በፊት የተነገረላቸው የትግነግ ተዋጊዎች እስካሁን በአፋር ግንባር ይህ ነው የሚባል ማስመዝገባቸውን አልተቆሙም።
የጦርነት መረጃ ሁሉ እንደማይነገር የሚገልጸው መንግስት የመከላከያ ሃይል ከድካምና ከባይተዋርነት አገግሞ ሰንጋ እየበላ ደጀን መካከል ሆኖ መዋጋት ከጀመረ አንስቶ በትህነግ ላይ ከፈተኛ የሚባል ሰባዊ ቀውስ እያደረሰ ነው።
ለደጋፊዎቻቸው ብርታት ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ድል ዘመቻ የሚያስተጋቡት የትህነግ ደጋፊዎች በተመሳሳይ ” ትግራይ እያለቅች ነው” የሚል የማህበራዊ ዘመቻ ጀምረዋል። በተመሳሳይ ትህነግ አሸባሪ መሆኑንን የሚያበስር ሎጎ ኢትዮጵያን የሚወዱ ዜጎች እያሰራጩ ነው።
ትህነግ ቆቦን መያዙን ሲያስታውቅ ካሰራጨው ፎቶ በተለይ ቆቦን ስለመነጠቁ ለደጋፊዎቹ ያለው ነገር የለም። በግንኙነት መረጃውን ከመስማት ውጪ መንግስት ቆቦ ስለመያዟም ሆነ ስለመለቀቋ ያለው ነገር የለም። አቶ ተሻገር ዛሬ ባሰሙት የክተት ጥሪ ‘ ስለወታደራዊ ውሎ በዚህ ገባን ወጣን እያልን መናገር አያስፈልግም። ይህን አሸባሪ ግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናተፋዋለን ” ማለታቸው ይታወሳል።
መከላከያ አሁን ላይ በትግራይ ክልል ውስጥ ገብቶ መዋጋት ያቆመ ሲሆን የትህነግ ሃይል ሊያተቃ ሲመጣ አፈግፍጎ አመቺ ቦታ ላይ ሲደርሱ በሂሊኮፕተር እያሳደዱ እንደሚመታቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።

- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ