ማንኛውም የተቀመጠውን መመሪያ የሚጥስ የአውሮፕላን አብራሪም ሆነ ኦፕሬተር ለሚደርሰው አደጋ ሃላፊነት እንደሚወስድ የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስጠንቅቋል፡፡
Ethiopia Current Issues Fact Check የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ በማህበራዊ ትስስስ ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ፣ ቀደም ሲል ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የአየር በረራ መረጃ ማሳወቂያ (NOTAM& AIP SUP) ቁጥር A0166/21 እና AIP SUP A04 ,2021) መተላለፉን አስታውሷል፡፡
በተላለፈው መመሪያ መሠረትም ማንኛውም የአውሮፕላን አብራሪም ሆነ ኦፕሬተር የተቀመጠውን መመሪያ ከጣሰ ለሚደርሰው አደጋ ሃላፊነቱ የራሱ የጣሰው አካል መሆኑንን መግለጫው አስታውቋል።በስምምነቱና ማስታወቂያው መስረት በኮድና በቁጥር ተሰፍሮ በቀረበው ማሳወቂያ፣ መንግስት ይህን በማያከብሩ ላይ ለሚወሰደው እርምጃ ሃላፊነት እንደማይወስድ ለምን እንዳስታወቀ ምክንያቱን አላብራራም።
በማስታወሻው በይፋ ባይገለጽም በርዳታ ስም በቀጥታ ወደ ትግራይ በረራ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥያቄ መቅረቡ ይታወሳል። መንግስት ጥያቄውን ተቀብሎ፣ ትብብር እንደሚያድርግ አስታውቆ እንዳለው ” ማንኛውም በረራ አዲስ አበባ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሶ ፍተሻ እንዲደረገበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት የሚከናወን ነው። በዚሁ መግባቢያ መሰረት የዓለሙ የምግብ ድርጅት አውሮፕላን ከአንዴም ሁለቴ አስፈላጊው ፍተሻ ተደርጎበት መቀለ ደርሶ መመለሱ መዘገቡ ይታወሳል።
ስምምነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ለምን መንግስት ይህን መግለጫ ለማውጣት እንደፈለገ ግልጽ ባያድረግም ስምምነቱን የመጣስ ሙከራ ስለመኖሩ አመልካች እንደሆነ ከግምት በላይ አስተያየት እየተሰጠ ነው። መንግስት መመሪያውን በጣሱ አካላት ላይ እርምጃ ከውሰደ ለጣልቃ ገብነት መነሻ ምክንያት ለማድረግ ታስቦ እንደሆንም ተመልክቷል።
It is to be recalled that as of June 30th 2021, a NOTAM& AIP SUP has been issued with reference number (A0166/21 and AIP SUP A 04 2021) by the Ethiopian Civil Aviation Authority. Therefore, violations against the above NOTAM will result in high risk to any operators and/or pilots. Entities violating the issued NOTAM therefore assumes full responsibility for any related actions.

- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. … Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል