የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ።የአገር መከላከያ ሰራዊት ትግራይን ለቆ ከወጣ ጀምሮ የራያ አዘቦ ተወላጆች የሆኑ በርካታ ሰዎች መገደላቸውንም ፓርቲው አስታውቋል።
በተጨማሪም ከ30 ሺህ በላይ ከአካባቢያቸው ተሰደዋል።የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጥጋቡ ጎበና እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የራያ አዘቦ መኾኒ ከንቲባ አቶ አለ በርዎ ከኢዜአ ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል።የራያ አዘቦ ህዝብ ባለፉት ሶስት ዓመታት አገራዊ ለውጡን ተቀብሎ የህዝቡን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል።
ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ከማንም በላይ ጭቆና ሲደረስበት እንደነበር አስታውሰው፤ ክልሉን መከላከያ ከያዘው ጀምሮ በተለይ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ ወደ እርሻው መግባቱን ተናግረዋል።ሆኖም በአሁኑ ወቅት መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን የተናጠል ተኩስ አቁም ውሳኔ ተከትሎ ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን ገልጸዋል።
የትግራይ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን እንዲያከናውንና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ መንግስት ያደረገው መልካም ተግባር የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ግድያና ሰቆቃ እየደረሰበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ክልሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር እያለ የራያ አዘቦ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው፤ “አሁን ከአካባቢው መልቀቁን ተከትሎ ችግር ውስጥ በመግባቱ መፍትሄ ያስፈልገዋል” ብለዋል። የራያ አዞቦ ህዝብ ከዚህ የከፋ ጉዳት ከማስተናገዱ በፊት መንግስትና መከላከያ እንዲደርስለትም መጠየቁን ኢዜአ ዘግቧል።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ