የዕርዳታ እህል ነው የጫንኩት ያለው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ከሱዳን በቀጥታ አሰልፎ ወደ ኢትዮጵያ ያስገባቸውን ዘጠኝ ከባድ መኪኖችን ” አላስፈትሽም” በማለቱ ፖሊስ አስቁሟል። ” መንግስት እርዳታ አስተጓጎለ” የሚል መግለጫ ይጠበቃል።
በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ተገቢ የጥንቃቄ እርምጃ ለመውሰድ ሲል መኪኖቹን አስቁሞ ፍተሻ ላድረግ ማለቱን ያስታወቁት በስፍራው ያሉ እማኞች ናቸው። የዕርዳታ ቁስ ጭነዋል የተባሉት ሎቤድ ተሳቢዎች ከሱዳን ተነስተው ወደ ትግራይ ለመሄድ፣ በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ ፍላቂት ከተማ ከደረሱ በኋላ ፖሊስ የጸጥታና የጥንቃቄ ጥያቄ ያነሳው።
በአስቸኳይ ፍተሻ ተደርጎ እርዳታው ለህዝቡ እንዲደርስ የተጠየቁት ክፍሎች ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የፍላቂት ከተማ ፓሊስ ዘጠኙንም የ WFP ተሽከርካሪዎች ከሁለት ማርክ 2 አጃቢ መኪኖች ለጊዜው ባሉበት ሳይነቀሳቀሱ እንዲቆዩ አድርጓል።
WFP ከትሀነግ አመራሮች ጋር የድርጅቱ መርህ በማይፈቅድው ደረጃ በገሃድና በድብቅ እየፈጸመ ያለው ተግባር ለጥርጣሬው መነሻ መሆኑን ተመክቷል። በፈተሻ መሳሪያ ከተገኘ የዓለም ምግብ ድርጅት በአደባባይ በማስረጃ ስለሚወገዝ የአካባቢው አስተዳደር ከመንግስት ጋር ተነጋግሮ መከናወን ያለበትን አከናውኖ ጉዳዩን እልባት እንዲያበጅለት ዜናውን ያሰራጩ ገልጸዋል።
ዜናው በማህበራዊ ገጾች የዓይን ምስክሮች ካሰራጩት ውጭ ከመንግስት ወገንም ሆነ ከዓለም ድርጅት በኩል እስካሁን በገሃድ የተባለ ነገር የለም። ትህነግ እርዳታን ሃይሉን ለማደስ እንደሚጠቀምበት ልምዶች ምስክር መሆናቸው በተደጋጋሚ የተባለ ጉዳይ ነው። ድርድርን አስመልክቶም ቅድሚያ ያስቀመጠው ነጻ በረራና የየብስ ኮሪዶር መሆኑ ይታወሳል።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ”… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል