” የሰማ ዕረፍት” ሲሉ የትህነግ ሃይል የገደላቸውን ወገኖቻቸውን ምስል ይዘዋል። ህጻናት የተፈናቀሉ ስደተኞች ቢሆኑም የዓለሙ የስደተኞች ድርጅት አንዳችም ድጋፍ እንዳላደረገላቸው በጽሁፍ ያሳያሉ። ስደተኞች እንጂ ወንጀለኞች አለመሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት እንዲያይላቸው፣ እዲሰማ ደጁ ቆመዋል። የኤርትራ ተፈናቃይ ሰደተኞች።
አንድ ጠይው ሕጻን ማስክ አድርጋ ” እነዛ በትግራይ ካምፕ ያሉ ባስቸኳይ ወደ ሰላማዊ ስፋር ይዛወሩ” ስትል ትጠይቃለች። ከጎኗ ” እኛ ስደተኞች ነን። እኛም እንደ እናንተ ሰዎች ነን” ትላለች። በርካታ ልብ የሚነኩ መፈክሮች የያዙት የኤርትራ ስደተኞች በተባበሩት መንግስታት ቢሮ ደጅ ቆመው ” የህግ ያለ” ሲሉ ላየ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢለኔ ስዩም ” ዓለም ትህነግን ዝም አለው። ለለም፣ ለምን፣ ለምን…?” ሲሉ የጠየቁት ጥያቄ አግባብ መሆኑንን ይረዳል። ግን ለምን የኤርትራ ስደተኞች በዓለሙ የስደተኞች ካምፕ ስር ሆነው ሳለ ይገደላሉ? ይንገላታሉ? ይዘረፋሉ? ይፈናቀላሉ? በሚደርስባቸው ግፍ መጠንስ ስለምን ተቆርቋሪ አጡ? የቢለኔ ስዩም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ጥያቄ ነው።

በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በትግራይ ክልል ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና እንግልት በመቃወም ሠላማዊ ሠልፍ ሲያካሂዱ ያነሱት ጥያቄ ይህንኑ ” ለምን ዝም እንባላለን?” የሚለውን ነው። ኤርትራዊያኑ ስደተኞች በአዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት መስሪያ ቤት ተገኝተው ላሰሙት ጩኸት የተሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ አልታወቀም።
በኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ የሚደረግ ጥቃት ይቁም’፣ ‘ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድምፃችንን ይስማ’፣ እና ሌሎችንም መፈክሮች በመያዝ የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ ክልል የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ከሚደርስባቸው ግፍና በደል እንዲታደጋቸውም ጥሪ አቅርበዋል።ስደተኞቹ ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለመንግስታቱ የስደተኞች ድርጅት በደብዳቤና በአካል በመገኘት መልዕክት ብናስተላለፍም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ ምሬታቸውን አሰምተዋል።
በትግራይ ክልል በሚገኙ ስደተኞች ላይ ግፍና እንግልቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስደተኞች እየተገደሉና በየጫካው በሽሽት ላይ ያሉትም ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ ይሰጠን ሲሉም ጠይቀዋል።
በሠላማዊ ሠልፉ ላይ አካል ጉዳተኞች፣ ሕፃናትና አዛውንት መሳተፋቸውን ኢዜአ ያተመው ምስል ያስረዳል። አሜሪካ በትናትናው ዕለት የኤርትራ ስደተኞች ጉዳይ እንደሚያሳስባት አምጣ፣ አምጣ ማስታወቋ አይዘነጋም።

- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል