“አሸባሪ” የሚል መዕረግ ተሸልሞ ወደ መቀለ የተመለሰው የትህነግ ቡድን ” ፈሪና ጀግና” በሚል እተፈራረጁ መሆኑንን በአሜሪካ የድርጅቱ ዋና ደጋፊ መናገራቸው ተሰማ። በረሃ የወረዱት ” ጅግና” ሲባሉ፤ ከተማ ተደብቀው የነበሩ ” ፈሪ” እየተባሉ ነው።
ትህነግ ከበረሃ ወጥቶ ወደ መቀለ ሲገባ ከተደበቁበት ከወጡት መካከል ዳንዔል ብርሃኔ ይገኝበታል። የድርጅቱ ዋና ደጋፊ እንዳሉት እነ ዳንኤል የሳተላይት ስልክ እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል። ለዚህም ምክንያቱ ” ፈሪ” በመሆናቸው ነው።
ለወትሮው ከማህበራዊ ገጽ የማይጠፋውና ወደ መቀለ ከሄደ በሁዋላ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በመስደብ፣ በማሽሟጠጥና በማውገዝ ስራ ተሰማርቶ የነበረው ዳንዔል፣ መንግስት እንዴት እንደሚቀየር፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዴት የዓለሙ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዴት እንደሚቀርቡ፣ ጦርነቱ ከሁለት ሳምንት በላይ እንደማይፈጅ በተደጋጋሚ በማስረዳት ቀዳሚ ነበር።
ተደብቆ ሕይወቱን ያተረፈው ዳንዔል ስልክ ፈልጎ ማጣቱን ከላይ የተገለጹት የትህነግ ዋና አባል በስሞታ ደረጃ ከሌሎች መስማታቸውን አስታውቀዋል። ቀደ ባለው ጊዜ ዳኒ የጌታቸው አሰፋ ወገን እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነገር ነበር። “የደህንነቱ ሹም አለመኖራቸው ዳኒ ስልክና ኢንተርኔት ብርቁ ሆነ” ሲል የሰማውን ወሬ ያጋራን የአሜሪካ ተባባሪያችን ነው።
እንደ ዳኒ ሁሉ በርካታ የተደበቁ የነበሩ ” ፈሪ” ተብለው ፊት እንደተነሱ ከመቀለ መረጃ ያላቸው አስታውቀዋል።

- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል።… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ”… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ