ትናንት በአፋር በኩል ትንኮሳ ፈጽሞ ሜይዴይ የሚባለው ሀይሉ የተደመሰሰበት አሸባሪው ህወሓት ህጻናትን በጦርነቱ ማሳለፉን የሚያረጋግጥ ተጨማሪ መረጃዎች እየወጡ ነው። በጌታቸው ረዳ ቅስቀሳ እየተማገዱ ያሉ ሕጻናትን ያዩ የትግራይ ተወላጆች ቁጣቸውን እያሰሙ ነው።
በትናንትናው እለት በአፋር ክልል አለሌ ሱሉላ በኩል የመጣውና የጁንታው ሜይደይ ተብሎ የሚጠራ ሀይል በሙሉ መደምሰሱ የተለጸ ሲሆን፤ ጁንታው ህጻናትን በጦርነቱ አሰልፎ እንደነበር በቁጥጥር ስር ከዋሉ ህጻናት ምርኮኞች ማረጋገጥ ተችሏል።
በቆቦ በኩል ሲተነኩስ የነበረው የአሻባሪው ሀይል እንደተደመሰሰ፤ ጁንታው ያሰማራቸው በርካታ ህፃናትም መማረካቸውን ምንጮቹን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ትናንት ምሽት ላይ መዘገቡ ይታወሳል። በዚህ ግንባር ተሰልፈው በሀገር መከላከያ ሰራዊትና በአፋር ልዩ ሃይል ከተያዙ ህጻናት መካከል የተወሰኑት ህጻናት ምስል ከስር ተያይዞ ቀርቧል።
ጁንታው ህጻናትን ለጦርነት እያሰለፈ መሆኑ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ቢሆንም ዓለም አቀፉ ማህበሰብ እስካሁን በይፋ ያለው ነገር የለም። ትናንት ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ አሸባሪው ህወሓት ህጻናትን ለውትድርና እየተጠቀመ መሆኑን በመጥቀስ የባይደን አስተዳደር ምን ምላሽ አለው በሚል ጥያቄ የተነሳላቸው የአሜሪካ የነጩ ቤተመንግስት ቃል አቀባይ ጥያቄውን ሳይመልሱት ማለፋቸው ይታወሳል።
ዞባ ተምቤን እንዳለው ጌታቸው ረዳ ለፍርድ መቅረብ አለበት። ሲያስረዳም “የትግራይ ህጻናት ለምን ይጨፈጨፋሉ? ተጠያቂው እሱ ነው” ብሏል። ዞባ ይህን ይበል እንጂ ትህነግ ሓጻናትን ለጦርነት ሲያበረታታና ሲያዘገጅ የነበረው አስቀድሞ በመሆኑ ሁሉም የዚህ ወንጀል ተተያቂ መሆን እንዳለባቸው ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችና ተሰሚነት ያላቸው ወገኖች ቀስ እያሉ ተቃውሞ ከሚያሰሙት ጎን እየሆኑ ነው።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል።… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ”… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ