በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ምግብን በመመረዝ የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ የሶስት ሰዎች ህይወት እንዲጠፋ በማድረግ ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።
የወረዳው ፖሊስ መምሪያ ምክትል ኃላፊ ኢንስፔክተር ታምሩ ባይሣ ዛሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤በወረጃርሶ ወረዳ አዋሬ ጐልጄ ቀበሌ ልዩ ስሙ በዳዳ ገብርኤል አካባቢ ነዋሪ የሆኑት የእነዚህ ሰዎች ህይወት ያለፈው ሰኔ 21/2013 ዓ.ም ነው።
ህይወታቸው ያለፈው በዕለቱ ጠዋት ቁርሳቸውን ለጊዜው በውል ባልታወቀ ሁኔታ የተመረዘ የእንጀራ ፍርፍር በመመገባቸው ሳይሆን እንዳልቀረ አስረድተዋል።
ሟቾቹ የ50 እና 14 ዓመት እድሜ ያላቸው ሁለት ሴቶች እና የሶስት ዓመት ወንድ ህፃን ልጅ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ከዚህም ሌላ ፍርፍሩን የበሉ ውሻና ድመት መሞታቸውን አመልክተዋል፡፡
ፖሊስ በወንጀሉ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገባቸው መሆኑን ኢንስፔክተር ታምሩ አስታውቀዋል፡፡ የሟቾቹ አስክሬን ለምርመራ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ አቤት ሆስፒታል እና ተመርዟል የተባለው የምግቡ ናሙና ደግሞ ለብሔራዊ የሥነ-ምግብና መድሀኒት ምርምር ኢንስቲትዩት ተልኮ ውጤት እየተጠበቀ ነው ብለዋል፡፡
TIPS
The Wars We Still Can Stop
Ethiopia: Israel Foreign Minister Says His Country Wants to Be Part of Ethiopia’s Success
A Nation Silenced: How the 1993 Referendum Stripped All Ethiopians of Their Sea
The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
Away from the global spotlight, Eritreans are trapped in a garrison state
Testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s
Ethiopia-Eritrea Tension: A Volatile History that Never Truly Ended – Could Assab Become Africa’s Crimea?
“As an outlier among the five tplf leaders, I wasn’t part of the armed struggle tradition”
Former Tigray fighters say no to war
Don’t Risk Your Future: The United States Cracks Down on Illegal Immigration
Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation
Ethiopia and Eritrea Slide Closer to War amid Tigray Upheaval
Sea Outlet Serious and Unabated Agenda for Ethiopia: Retired Lieutenant General Yohannes
Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
Egyptian, Eritrean FMs reject involvement of non-bordering countries[Ethiopia] in Red Sea security
Ethiopia, Creditors Agree on $8.4 Billion Debt Restructuring