አዲስ አበባ፦ መላው የአማራ ህዝብ አሁን እያጋጠመው ያለው አደጋ የታሪክና የማህበራዊ ክብር እንዲሁም የማንነት ጉዳይ በመሆኑ አጠቃላይ ጥቃቱን ለመመከት አስቸኳይ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ።
አብን ትናንት ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ፣መላው የአማራ ህዝብ አሁን እያጋጠመው ያለው አደጋ የታሪክና የማህበራዊ ክብር እንዲሁም የማንነት ጉዳይ መሆኑን በመረዳት አጠቃላይ ጥቃቱን ለመመከት አስቸኳይ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
የአማራ ወጣቶች በየአካባቢያችሁ በመምከርና በመደራጀት፣ ራሳችሁን በማስታጠቅ ለሁለንተናዊ ዘመቻ ራሳችሁን እንድታዘጋጁ፣በሁሉም አካባቢዎች ያላችሁ የአማራ ፋኖዎች በአሁኑ ሰዓት ህዝባችን ያጋጠመውን የህልውና ትግል ለመቀልበስ በግንባር ለመንቀሳቀስ ፈጣን ዝግጅት እንድታደርጉ ብሏል።
መላው የአማራ ህዝብ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅና በተለይም በመካከላችን ሆነው ሴራና ጥቃት የሚያቀናብሩ፣ በሰርጎ ገብነት መረጃ ለጠላት የሚያቀብሉ አካላትን በንቃት በመከታተል የማክሸፍና የመቆጣጠር ሥራ እንዲያከናውን ጥሪ አቅርቧል።
በተለያየ የአመራር ጥፋትና ጥሰት ያላግባብ ተገፍታችሁ ከፀጥታና ከወታደራዊ አመራ ርነታችሁና ሙያችሁ ውጭ የተደረጋችሁ የአ ማራ ልጆች በሙሉ ህዝባችሁን ለመታደግ የሚደረገውን ታሪካዊ እንቅስቃሴ ለመቀላቀል እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አሳስቧል።
አብን በመግለጫው ፣ሂደቶችን በአስተ ውሎት እየተከታተልንና መረጃ እየሰበሰብን በመቆየት ነገሮች ይሻሻላሉ በማለት ብንጠብቅም ችግሮቹ በፍጥነት ሲወሳሰቡ በማየታችን ለህዝባችን ህልውና ይህንን ጥሪ ለማድረግ ተገደናል ብሏል።
መላው የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የህል ውና አደጋ ለመቀልበስ ለሚደረገው ሁለንተናዊ ዘመቻ በትጥቅና ስንቅ አቅርቦት እንዲሁም በደጀንነት ርብርብ እንዲደረግ የጠየቀው አብን ፣ የህልውና ዘመቻውን በሙሉ እንዲቀላቀሉ እና እንዲያስተባብሩ ለሁሉም የንቅናቄው አባላትና አመራሮች ትዕዛዝ ማስተላለፉንም አስታውቋል።
በጋዜጣው ሪፖርተር
አዲስ ዘመን ሐምሌ 7/2013
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ”… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል
- ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂበኳታራውያን ባለሀብቶች የሚተዳደረው የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ያለውን ተደጋጋሚ የበላይነት በአውሮፓ ለማሳየት ከአሰልጣኞች አስከ ስመ ጥር የእግር ኳስ ኮከቦች ወደ… Read more: ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂ