Invading #Afar and killing Afars will only make Afars stronger but will freeze the relations between brotherly people of Afar and Tigray. As your lies fades away the truth is coming forward. We know the truth and you're responsible! 3/3.@UNICEF @PowerUSAID@SecBlinken @WFP pic.twitter.com/nH86NwCRvE
— Kontie Moussa_ኮንቴ ሙሳ (@kontiem) August 11, 2021“አፋርን መውረርና የአፋርን ህዝብ መጨፍጨፍ ጠንካራ ያደርገናል። በሌላ በኩል ደግሞ በአፋርና በትግራይ ክልል ሕዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት ይገለዋል። ቅጥፈታችሁ እየወየበና እየደበዘዘ፣ እውነት ወደ አደባባይ እየመጣች ነው። እውነቱን እናውቀዋለን። ተጠያቂዎቹ እናንተ ናቹህ” ሲሉ አምርረው ያስታወቁት ዶ/ር ኮንቴ ሙሳ ናቸው።
ዶክተር ኮንቴ ይህን ያሉት ጌታቸው ረዳ ” ከደሙ ንጹህ ነን” በሚል ጭፍጨፋውን አሸባሪው ትህነግ ሳይሆን መንግስት እንድፈጸመው ጥቅሰው በቲወተር ገጹ ላሰራጨው ሲመልሱ ነው።
ዶ/ር ኮንቴ ጭፍጨፋው ሲፈጸም ጋሊኮማ ላይ የትህነግ ሃይል ማሳከር ሲፈጽም በስፍራው የመንግስት ሰራዊት እንዳልነበር አስታውቀዋል። በትናንትናው ዕለት ስምንት የቤተሰብ አባላት በሚዘገንን ሁኔታ መጨፍጨፋቸውን ይፋ ባደረጉበት የቲውተር አውዳቸው ላይ እንዳስታወቁት የዩኒሴፍን ተዓማኝነት ሁሉ ጥርጣሬ ውስጥ እንደሚያስገቡ አመላክተዋል።
የተደረገውን ተኩስ አቁም ተከትሎ ለምን ጉዳይ አፋርን እንደወረረና፣ በምን ምክንያት 240 ንጹሃንን ከተጠለሉበት ድረስ ዘልቆ ለመጨፍጨፍ እንደወሰነ ትህነግ እስካሁን በገሃድ በዝርዝር ያለው ነገር የለም። ይሁን እንጂ ዶክተር ኮንቴ እንዳሉት በስፍራው ያልነበረውን የመከላከያ ሃይል አውግዞ አጭር የቲውተር ሃሳብ ለጥፏል።
አንድ መቶ ሰባት ህጻናት የተጨፈጨፉበት ትዕንት ቆስለው ህክምና በማድረግ ላይ ብሚገኙ አካላት ምስክርነት እየተሰጠበት ቢሆንም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እስካሁን ምንም አስተያየት አልሰጠበትም።
ትግራይን ሄዶ የማየት እድል ያልነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከማንና እንዴት እንደሚያገኘው ግልጽ ሳይሆን ተከታታይ መረጃ ሲያከታትል እንዳልነበረ፣ ዛሬ በአፋር ሆስፒታል ያሉ እማኞችን ሄዶ ለማነጋገር ይህን ያህል ጊዜ መውሰዱ የዶክተር ዳንዔልን አቋም ይበልጥ ጥያቄ ውስጥ አስገብቷል።
ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች ትህነግ ጭፍሮቹን አሰማርቶ አስገድዶ መድፈር ፈጽሟል። ሕጻናትን ጭፍጭፏል። ዝርፊያ አካሂዷል። ከፍተኛ የተባለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል።
ዛሬ ረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ወደ ስፍራው ቡድን መላኩን አውስቶ፣ ስጋት እንደገባው ጠቁሞ አጭር ጥሪ አሰምቷል። ድርጅቱ ትህነግ በወረራቸው አካባቢዎች ስለተፈናቀሉ፣ ስለተገደሉና ስለተዘረፉ ሰዎች እስካሁን ያለው ነገር የለም። ከንግሊዝ ተመልሰው ድርጅቱን የሚመሩት ዶ/ር ዳንኤል የማይካድራውን ጭፍጨፋ ሪፖርት ከዳፈኑ በሁዋላ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ተዓማኝነታቸው እየወረደ እንደሚገኝ በርካቶች እያወሱ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፋር ክልል መንግስት በግፍ ለተጨፈጨፉት ወገኖች የሶስት ቀን ሃዘን አውጇል። ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ አድርጓል።
ዶክተር ኮንቴ የተቃዋሚ ፖለቲካ አመራር፣ ኢትዮጵያዊ አቋማቸው ላይ መዛነፍ የሌላቸው፣ ህዝብ የሚወዳቸው ፖለቲከኛ ናቸው።
በአፋር ንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ በተፈጸመ ማግስት መንግስት የዜጎቹን ሰላም ለማስጠበቅ ሲል በይፋ የማጥቃት እርምጃ እንዲወሰድ መመሪያ እንደሚሰጥ አስቀድመው የገለጹ የአሜሪካ ባለስልጣናት ነበሩ።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and the ongoing tensions… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን በቅጡ የሚገነዘቡ ምሁራን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ