አሸባሪው ህወሃት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎና በጎንደር የህዝቡን የኢኮኖሚ መሰረቶች ማውደሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ህዝቡን ለመከራና ስቃይ በመዳረግ ዳግም ወደ ፖለቲካ ስልጣን ለመምጣት አደገኛ ሙከራ ውስጥ የተዘፈቀው ላለፉት 27 አመታት ስልጣን ላይ የነበረው አሸባሪው ቡድን፤ አብዛኛው የትግራይ ክልል ህዝብን ከሴፍቲኔት ተረጅነት እንኳን ሊያላቅቅ አልቻለም፣ ቡድኑ ለክልሉ ህዝብም ደህንነት ያለውን ግዴለሽነት በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሸባሪ ቡድኑ በወረራቸው የሰሜን ወሎና ጎንደር አካባቢዎች ያደረሰው መጠነ ሰፊ ውድመት የአማራ ህዝብ ጠላትነቱን ዳግም ያስመሰከረበት መሆኑን ገልጿል።
በወረራ ከያዛቸው አካባቢዎች የሚወጡ ሪፖርቶች እንዳመለከቱት የብዙ ቤተሰቦች የኢኮኖሚ አቅሞችን አውድሟል፤ በወረራቸው አካባቢዎች ያሉ አርሶ አደሮች የአሸባሪው ታጣቂዎች የደረሱ ሰብሎችን እየዘረፉ ማመልከታቸውን ጠቅሷል።
“አርሶአደሩ ያከማቸው እህል ተዘርፏል የቀረውም እንዲወድም ሆኗል፤ የእርዳታ እህል ማከማቻ መጋዘኖች የአሸባሪው ቡድን የዘርፋ ሰለባ ከመሆናቸው ባሻገር ከተረጂዎችም ይቀማል” ብሏል መግለጫው፡፡
ቡድኑ ያስከተለው መጠነ ሰፊ ውድመት በግለሰብ ላይ ብቻ ሳይሆን እንደማህበረሰብ የህዝብ መገልገያዎችን የህፃናት መዋያዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች፣ ባንኮች፣ የጤና ማዕከላት፣ ሆቴሎችና ሎሎችም ተቋማት ወድመዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and the ongoing tensions with Iran, its Foreign Minister Gideon Sa’ar found more time to visit Ethiopia. This visit underscores the importance of what the Israeli occupation minister discussed, and opens the… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን በቅጡ የሚገነዘቡ ምሁራን የራስ ዱሜራን ጉዳይ ወደ አደባባይ ይዘውት ቢመጡ እንዴት ጥሩ ነበር ምክንያቱም መልካም ሀሳቦች ሲጠራቀሙ ሀገር ያጸናልና! በጅቡቲ ላይ ወሳኝ ጥያቄ ማንሳት የሚያስችሉ ታሪካዊ አጋጣሚዎች የነበሩት ደርግ እና በኤርትራ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።ከትግራይ ጊዜያዊ መንበራቸው በአመጽና በጠመንጃ ኃይል እንዲወገዱ የተደረጉት አቶ ጌታቸው ውስን ያሉዋቸውን ጄነራሎች ስም እየጠቀሱና በጥቅሉ ተጋባራቸው “የብረሃን ስራ በብርሃን ነው” እንደተባሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ ስፔሻሊስት ስለነበርኩ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም ” – የራሱን ሰርግ አቋርጦ ቀዶ ሕክምና በማድረግ ሕይወት የታደገዉ ዶክተር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሌ ከተማ አስተዳደር የበሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
በግንባታ ሂደት ላይ ያለው የአዋሽ ወልዲያ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድ ፕሮጀክት ሃላፊነት በማይሰማው አሸባሪ ቡድን የጥቃት ሰለባ ሆኗል ፡፡
“ሽብር ቡድኑ የሚያስከትላቸው መጠነ ሰፊ ውድመቶች ለትግራይ ህዝብ የሚፈይድለት ነገር እንደሌለ ይታወቃል፤ ይልቁንም የትግራይና የአማራን ህዝብ ወደ ባሰ ስቃይና እንግልት ያስገባል” ሲል ሚኒስቴሩ አመልክቷል፡፡
የሽብር ቡድኑ በሰሜን ወሎ እንዲሁም በጎንደር የፈፀመውና እየፈፀመ ያለው ውድመት በፖለቲካው አለሁ ለማለት የሚደረግ የመጨረሻው መፍጨርጨር እንደሆነም ነው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በችግር ውስጥያሉና እገዛ የሚሹ በሰሜን ወሎና ጎንደር ያሉ ህዝቦችን ትኩረት እንዲሰጣቸው የጠየቀው መግለጫው፤ ወራሪው በያዛቸው አካባቢዎች ያሉ ዜጎች የተፋጠነ የሰብአዊ እርዳታ እንዲደርሳቸው ጥሪ አቅርቧል።
Ena