ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በጥምረት ሲዋጉና ሲዋደቁ የነበሩት ፋኖዎች ወያኔ የአማራን ንብረት ዘርፎ መቀሌ ከገባ በኋላ የዶ/ር አብይ መንግስት ሆን ብሎ “ህወሓትን ለመታደግ ሲል መቀሌ አንገባም አለ” የሚል ጥያቄ ሊያነሱ ይችላሉ?>> ከሚለው ጥያቄ በስተጀርባ የሆነ እኩይ እሳቤ አለ።
መቼም “የአማራ ንብረት ተዘርፎ ኦሮሞ ዝምታን መረጠ ወይም የተዘረፈውን ንብረት ለማስመለስ ፍላጎት የለውም” የሚሉ በብሄር እይታ የተንሻፈፉ ምልከታዎች አይጠፉም። ይሄ የወያኔ ዘመን ጠባሳ ነው። ይሄን ጠባሳ እያከኩ ቁማር የሚጫወቱት ወይ ወያኔዎች ናቸው አሊያም ደግሞ በማወቅ ሆነ አለማወቅ የእነሱን እኩይ ዓላማ የሚያስፈፅሙ ባንዳዎች ናቸው። የአማራ ወጣት የወደመውን አከባቢ መልሶ ለመገንባት የሚያውለውን አቅምና ግዜ በበቀል ስሜት ተነሳስቶ በቁጣና እልህ ወደ መቀሌ እንዲተምም የሚኮረኩሩ አይጠፉም።
ይሄ ኢትዮጵያ ሁሌም በጦርነት ስትታመስ እንድትኖር የሚሹ ጠላቶች ፍላጎት ነው። የአማራ ወጣቶች እና ፋኖዎች ደግሞ የተሻለ ልምድና ችሎታ የሚቀስሙበት ወታደራዊ ማሰልጠኛ ገብተው መከላከያን ቢቀላቀሉ ይመረጣል። ከዚያ በተረፈ ደግሞ የሁሉም ትኩረት ወደ መልሶ ማቋቋም እና ለዚህ አስፈላጊ በሆኑ ተግባራት ላይ መረባረብ አለበት።
ጉዳዩን “አማራ ተጎድቶ ኦሮሞ ዝም አለ” ዓይነት የወያኔን ጠባሳ በማከክ መከፋፈል ለመፍጠር የሚታትሩ ሰዎችን “መ/አ ጌታቸው ሞረዳ ለምን እና የት ሞተ?” ብላችሁ ጠይቋቸው። ወያኔዎች የሰሜን ዕዝን ሲያጠቁ በዋናነት የአማራና ኦሮሞ መኮንኖችን ለይተው አገቷቸው። ከእነዚህ ውስጥ አንዱ መ/አ ጌታቸው ሞረዳ ሲሆን ከትከሻው ላይ ደግሞ ወንድ ልጁ ነበር።
ጌታቸው ትውልዱ ኦሮሞ ነው። አያቱ “የማይጨው ዘማች” ናቸው። አባቱ ደግሞ በካራማራ የተዋደቁ ናቸው። መ/አ ጌታቸው ደግሞ የሰሜን ዕዝ አባል ነበር። ልጅና አባት ከህወሓት እገታ ካመለጡ በኋላ ወደ ወሊሶ በመሄድ አንድዬ ልጁን ለእህቶቹ አደራ ብሎ ወደ ጦር ግንባር ተመለሰ። በመጨረሻም መ/አ ጌታቸው ሞረዳ ልጁን ለእኛ አደራ ሰጥቶ በጋሸና ግንባር ሲዋጋ ተሰዋ። እንደ ጀግናው ገረሱ ዱኪ እንደ አያቱ እና አባቱ ለኢትዮጵያ አንድነት ሲታገል የወሊሶ ልጅ ወሎ ላይ ሞተ።
የሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ሌላ ምንም ሊሰጥ አይችልም። መ/አ ጌታቸው ሞረዳ የኢትዮጵያ ወታደር ነው። በጎሳ እና ብሔር ለሚያስቡት ደግሞ ጌታቸው ኦሮሞ ነው። ይህ የኦሮሞ ልጅ ጋሸና ላይ የሞተው እንደ አያት እና አባቱ ለሀገሩ ኢትዮጵያ ሲል ነው። ሞትና ጀግንነትን በብሔር ለሚያሰሉ ሰዎች ደግሞ “የወሊሶው ኦሮሞ ጌታቸው ሞረዳ ለወሎ አማራ ህዝብ ነፃነት ጋሸና ላይ ተዋድቆ ተሰዋ።
አንድ ልጁን ለእኛ አደራ ሰጥቶ የወደቀው “ቂሪው ትውልድ ከብሔር ጉጠት ከፍ ብሎ በኢትዮጵያ አንድነት እና አብሮነት ያስባል፣ የልጄን አደራ አይበላም” እኛ ተመልሰን የወያኔዎችን ጠባሳ እያከክን ኦሮሞ እና አማራ የሚል ጭቃ ማቡካት ከጀመርን፣ በእርግጥ እኛ ለቁም ነገር የማንበቃ ድኩማኖች ነን። እንደ ጌታቸው ሞረዳ ያሉ ሺህዎች ለአማራ ህዝብ መብት እና ነፃነት ህይወታቸውን ሰጥተዋል። የእነሱን መስዕዋትነት መዘንጋት የመጨረሻ ውርደት ነው።
Via seyum teshome – https://youtu.be/TBksCkN6qsc
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል
- ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂበኳታራውያን ባለሀብቶች የሚተዳደረው የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ያለውን ተደጋጋሚ… Read more: ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂ
- UAE Does Not Recognize the Decision of Port Sudan AuthorityMore stories US urges Americans to leave Russia “IMMEDIATELY”February 28, 2022… Read more: UAE Does Not Recognize the Decision of Port Sudan Authority