” ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የምንችለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ዉይይት ብቻ ነዉ። “- አቶ ሌንጮ ለታ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የሚዘጋጀዉ 18ኛዉ ዙር የጉሚ በለል የዉይይት መድረክ ” የብሔራዊ ዉይይቱ አንኳር ጉዳዮችና ሃገራዊ ፋይዳዉ” በሚል ርዕስ ተካሄዷል።
ለዉይይት መድረኩ የተዘጋጀዉን የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በኦሮሞ ፖለቲካ ዉስጥ ትልቅ ከበሬታ የሚሰጣቸዉ አንጋፋዉ ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ሲሆኑ በሃገራዊ ወይይቱ አስፈላጊነትና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ አንኳር ነጥቦችን አንስተዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የሚቻለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ወይይት ብቻ ነዉ ያሉት አወያዩ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ከጦርነት ይልቅ ሰላማዊ ወይይት ተመራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሃገራዊ ዉይይቱ ለኦሮሞ ህዝብ በጣም አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት አወያዩ ሃገራዊ ዉይይቱ በርካታ ድምጾችና ፍላጎቶች የሚንጸባረቁበትና የሚሰሙበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
እኩልነት በሌለበት አንድነትን መፍጠር አይችልም ያሉት አወያዩ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመፍጠር ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸዉን የሚመለከቱባትን ኢትዮጵያን መገንባት ይገባል ብለዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በሂደት እንጂ በአንድ ጊዜ መገንባት አይቻልም ያሉት አቶ ሌንጮ ለታ እንከን የሌለበት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መፈለግ የተሳሳተ አስተሳሰብ ነዉ ብለዋል።
አንዳንድ የዉይይቱ ተሳታፊዎችም ያለፉት ስርዓቶች ሲከተሉት የነበረዉ ፖለቲካዊ አስተሳሰብና ትርክት በሕዝቦች መካከል ልዩነት እንዲሰፋና አለመግባባት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
ያለፉት ስርዓቶች በህዝቡ መካከል ጥለዉ ያለፉትን የተዛቡና ተቀባይነት የሌላቸዉ ትርክቶችንና አስተሳሰቦችን በማረም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባት ሃገራዊ ዉይይቱ ትልቅ ድርሻ አለዉ ብለዋል።
ፖለቲከኞች: ጋዜጠኞች: አርቲስቶችና ምሁራን ለሃገራዊ ዉይይቱ ስኬት የድርሻቸዉን ሊወጡ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ተሳታፊዎቹን ያወያዩት የኦሮሚያ ዳያስፖራ ዳይሬክተር አቶ አሚን ጁንዲ ሲሆኑ በዉይይት መድረኩ ላይ ታዋቂ የኦሮሞ ፖለቲከኞች: የሚዲያ አመራሮችና ጋዜጠኞች: አትሌቶች: አርቲስቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። via OBN
ወንድማገኝ አሰፋ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው።… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል