አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በአማራና በአፋር ክልሎች በወረራ ገብቶ የፈጸማቸውን አሰቃቂና ዘግናኝ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያጣራ ግብረ ኃይል ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩን የፍትህ ሚኒስቴር ገለጸ።
በሚኒስቴሩ ፕሬስ ሴክሬታሪ ዳይሬክተር አቶ አወል ሡልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽብር ቡድኑ በለቀቃቸውና በወረራ ገብቶባቸው በነበሩ የአፋርና የአማራ ክልሎች ተንቀሳቅሶ የሚሠራ ግብረ ኃይል ተዋቅሮ የምርመራ ሥራ እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ደረጃውን የጠበቀ፣ ገለልተኛና የወንጀል ድርጊቱን ይዘትና ስፋት ሊያሳይ የሚችል ዐቃቤ ሕጎችና ፖሊሶች በተለቀቁ አካባቢዎች ተገኝተው ምርመራ እያደረጉ ይገኛሉ፤ ከወንጀል ድርጊቱ ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸውን ለማስረጃነት የሚጠቅሙ ግብአቶችን በማሰባሰብ ሰፊ የምርመራ ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
እንደርሳቸው ገለጻ፤ ከፌዴራል ፖሊስና ከክልሎቹ የፍትህ ተቋማት ጋር የተቀናጀው የምርመራ ቡድኑ በጋራ ምርመራውን እያከናወነ የሚገኘው በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ አካባቢዎች፣ በአፋር የተወሰኑ ወረዳዎች ላይ በመገኘት ነው።
አንዳንዶቹ ወንጀሎች ዓለም አቀፍ ወንጀሎች የሆኑ፣ በዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚቀርቡና ዓለም አቀፍ ድንጋጌን የጣሱ፤ የዘር ጭፍጨፋ፣ በሰዎች ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች በመሆናቸው ምርመራው ዓለም አቀፍ መሥፈርትን ያሟላ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።
ምርመራው ዓለም አቀፍ መሥፈርትን ማሟላቱ ወንጀለኞቹ በየትም አካባቢ ቢገኙም ለማስቀጣት በሚያስችል ሁኔታ የማስረጃ ማሰባሰብ ሥራ እንዲሠራ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
የሽብር ቡድኑ በአፋርና አማራ ክልሎች የተለያዩ ከተሞችና ወረዳዎች በወረራ በመግባት ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት ሲያደርስ መቆየቱን አስታውሰው፤ ሰዎች ከአካባቢያቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት መሆኑንና አሰቃቂ ወንጀሎችን ሲፈጽም መቆየቱንም አመልክተዋል።
ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ውጪ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ጭምር ኢላማ በማድረግ ጥቃት ሲፈጽም እንደነበረ፤ ያስታወሱት አቶ አወል አሸባሪ ቡድኑ በዓለም አቀፍ ሕግ ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ንጹሃንን፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሆስፒታሎችን እንዲሁም ሰላማዊ ሰዎች የሚገለገሉባቸውን ተቋማት ጨምሮ የጥቃት ኢላማ አድርጎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን አስታውሰዋል።
አሸባሪ ኃይሉ የመከላከያ ሠራዊት ከትግራይ ክልል ከመውጣቱ በፊትም በክልሉ ማይካድራን ጨምሮ በአማራ ክልል አጎራባች ወረዳዎች በርካታ ወንጀሎችን ሲፈጽም ነበር። በእነዚህ ቦታዎች የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንና የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች በቦታው ተገኝተው የሰብአዊ መብት ጥሰቱን ምርመራ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በዘላለም ግዛው
አዲስ ዘመን ታህሳስ 17 ቀን 2014 ዓ.ም
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል
- ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂበኳታራውያን ባለሀብቶች የሚተዳደረው የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ያለውን ተደጋጋሚ የበላይነት በአውሮፓ… Read more: ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂ