እንቡዝ ሰው የሚሠራውንና የሚናገረውን በጤነኛ አእምሮ መረዳት አይቻልም። ጤነኛ አእምሮ በተጠየቅ፣ በሞራል ሕግ፣ በመረጃ፣ በማስረጃ፣ በሐሳብ ሙግት፣ ወዘተ. ነው የሚረዳው። እንቡዝ ጋ ይህ ሁሉ የለም። መቅበዝበዝ፣ መስከርና ማበድ አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ሰብእና ነው።
በገድለ ተክለ ሃይማኖት የምናገኘው ሞተለሚ የተባለው የዳሞት ንጉሥ ለ25 ዓመታት እንቡዝ ሆኖ መኖሩን ይነግረናል። እንቡዝ የሚለውን ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙት፦ በቁሙ ልቡ የጠፋ፣ የተነበዘ፣ ነባዛ፣ ንብዝ፣ ቅብዝብዝ፣ ሰካር፣ እብድ፡፡ ሰብእ እንቡዛን፡፡ ብእሲት እንብዝት፡፡ እንቡዛነ ልብ ወድንቅዋነ እዝን (ኢሳ፳፭፡ ፭፡፡ ፶፬፡ ፮፡፡ መጽ፡ ምስ) ይሉታል። “ቅብዝብዝ ሰካር፣ እብድ” በሚሉት ነው አለቃ ለመበየን የሞከሩት።
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ታሪክ በጻፉ ጊዜ ሁሉ “እንቡዝ” የሚለውን “Insane” ብለው ነው የሚተረጉሙት። ኦክስፎርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት “Insane” የሚለውን ሲፈታ “in a state of mind which prevents normal perception, behaviour, or social interaction; seriously mentally ill.”
ይላል።
ሞተለሚ እንቡዝ ከሆነ በኋላ ያደረገው ነገር ይሄንን ትርጉም ያጠናክረዋል። ሥራው ያገኘውን ሁሉ ማጥፋት ነበር። ዓለም ልትጠፋ የሚገባት፣ ነገር ግን በደካሞች ምክንያት ሳትጠፋ የቀረች ትመስለው ነበር።
እንቡዝን ለመግለጥ አለቃ ኪዳነ ወልድ የተጠቀሙባቸውን ቃላት መመርመር የተሻለ ነገሩን ያሳየናል። መቅበዝበዝ – የመንፈስ አለመረጋጋት ነው። ይሄንን መጀመሪያ የተጠቀመው ቃየል ነው። ቃየል ወንድሙን በግፍ ከገደለ በኋላ መንፈሱ ያልተረጋጋ በመሆኑ ቅብዝብዝ ነበር። ወያኔም ገና ከጅምሩ መንገዱ የቃየል ነበር። ሰካር የአእምሮ መናወዝ ነው። በተጠጣ አስካሪ ነገር የሚመጣ ነው። ወያኔ ጎሰኝነት የሚባል አስካሪ መጠጥ ወስዷል። እብደት የልቡና መናወጽ ነው። ሥነ ልቡናዊ በሽታ ነው።
እንቡዝ ሰው የሚሠራውንና የሚናገረውን በጤነኛ አእምሮ መረዳት አይቻልም። ጤነኛ አእምሮ በተጠየቅ፣ በሞራል ሕግ፣ በመረጃ፣ በማስረጃ፣ በሐሳብ ሙግት፣ ወዘተ. ነው የሚረዳው። እንቡዝ ጋ ይህ ሁሉ የለም። መቅበዝበዝ፣ መስከርና ማበድ አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ሰብእና ነው።
ወያኔ እንቡዝ ስለሆነ ለጤነኛ ሰው የሚሰጡ ነገሮች አይስማሙትም። የሚናገረውና የሚሠራው ከሰብእና ውጭ የሆነው በንብዘቱ ምክንያት ነው። ለምን አደረገ? ብትሉ ንዴቱ እናንተን ያሳምማችኋል እንጂ ወያኔ አይሰማውም። ያንን ሁሉ ጥፋት ሠርቶ፣ ያንን ሁሉ ወጣት አስፈጅቶ ፈገግ ይላል። ለምን ቢሉ? እንቡዝሰ እንቡዝ ውእቱ። እንቡዝ ምን ብታደርጉት እንቡዝ ነው።
By Daniel kebret
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል
- ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂበኳታራውያን ባለሀብቶች የሚተዳደረው የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ያለውን ተደጋጋሚ የበላይነት በአውሮፓ ለማሳየት ከአሰልጣኞች አስከ ስመ ጥር… Read more: ያለ ኪልያን ምባፔ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ የደረሰው ፒኤስጂ
- UAE Does Not Recognize the Decision of Port Sudan AuthorityMore stories German Chancellor Olaf Scholz Due In Ethiopia For Two Days Working VisitApril 30, 2023 Gunmen open… Read more: UAE Does Not Recognize the Decision of Port Sudan Authority