ተከሳሽ ዘማ ደባሽ የተባለችው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 447/ለ/ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባታል፡፡
የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሿ የሌላውን ሰው ንጽህና እያወቀች ጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ በአራዳ ክፍለ ከተማ ጋንዲ ሆስፒታል ምርመራ ክፍል በመስከረም ወር 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 አካባቢ ቴዎድሮስ አበበ የተባለ ግለሰብ ቤት ውስጥ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትኖር “አልጋ አንጥፊ ብሎ ጠርቶኝ አስገድዶ ደፍሮኛል” በማለት ቃል ሰጥታ ተጠርጣሪው ተይዞ ጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀበት በኋላ ታህሳስ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ለኮልፌ ቀራኒዮ ፖሊስ መምሪያ ሴቶችና ህፃናት ምርመራ ክፍል ከቤቱ መውጣት ፈልጌ እንጂ አልደፈረኝም በማለት በድጋሜ ቃል የሰጠች በመሆኑ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ወይም መክሰስ ወንጀል ተከሳለች፡፡
ዐቃቤ ህግ በበኩሉ ተከሳሿ የተከሰሰችበትን የወንጀል ድርጊት እንደ ክሱ ሙሉ በሙሉ ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት በተከሳሿ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ይሰጥልኝ ሲል አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ በተከሰሰችበት ድንጋጌ ስር በዝርዝር ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት ጥፋተኛ ነሽ ብሏታል፡፡
ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ ፈጣን የወንጀል ችሎትም ታህሳስ 13 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ1 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እና አምስት መቶ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ