በደራሼ አካባቢ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንት በጥፋተኝነት የተጠረጠሩ ከ450 በላይ ግለሰቦችና 17 አመራሮችና የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እንዲሁም በደቡብ ኦሞ ዞን አካባቢ ደግሞ 650 የሚሆኑ ግለሰቦችና 11 አመራሮች በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉ ተገለጸ።ክልሉን የግጭት ማዕከል ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳው አመለከቱ።
ግንቦት 19 ቀን 2014 (ኢዜአ) በብሔር ስም እየነገዱ ክልሉን የግጭት ማዕከል ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሠላም ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳው አስታወቁ።
የደቡብ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ ክልላዊ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም የክልሉን ሠላምና ደህንነት በማስመልከት የተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት መድረክ በወላይታ ሶደ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በዚህ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው እንዳሉት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ያለፈው ሥርዐት ብልሹና ከፋፋይ አስተሳሰብ መሠረት ያደረጉ ግጭቶች መከሰታቸውን አስታውሰው በዚህም በርካታ ጥፋት ደርሷል ብለዋል።
ይህንን ጥፋት ለማስቆም በተለይ በክልሉ ክህዝቦች ጋር በቅርበት በተከናወኑ ስራዎች ባለፉት ሁለት አመታት በክልሉ አንፃራዊ ሠላም ማስፈን መቻሉንና በተገኘው ሠላም ወደ ልማት በመዞር ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን ጠቅሰዋል።
ሆኖም በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ላይ የተራዘሙ ግጭቶች እየተስተዋሉ ነው ያሉት አቶ ርስቱ በቅርቡ በደራሼ ልዩ ወረዳ አካባቢ የተከሰተው ግጭት የፀጥታ አካላትንም ጭምር ለአሰቃቂ መስዋዕትነት የዳረገ መሆኑን አውስተዋል።
በተለይም በደራሼ ፣ ኮንሶ ፣ ኧሌ እና አካባቢው ላይ ግጭቶችን ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ አካላት ቀጠናውን እያወኩ ፣ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እየገቱ እንደሚገኙ ገልጸው እነዚህ አካላት በብሔር ስም የሚነግዱና ክልሉን የግጭት ማዕከል የማድረግ ዓላማ ያነገቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የክልሉ መንግስት ባለፈው አንድ ወር እነዚህን አካባቢዎች ከማረጋጋት ባለፈ ሕግን የማስከበር ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው አሁንም በፀረ ህዝብ በሆኑት ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በደራሼ አካባቢ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንት በጥፋተኝነት የተጠረጠሩ ከ450 በላይ ግለሰቦችና 17 አመራሮችና የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እንዲሁም በደቡብ ኦሞ ዞን አካባቢ ደግሞ 650 የሚሆኑ ግለሰቦችና 11 አመራሮች በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል ብለዋል።
በኮንሶና ኧሌ በነበረው ግጭት እንዲሁም በስልጤ ዞን ለመቀስቀስ ተሞክሮ በነበረው የሐይማኖት ግጭት ምክንያት የተጠረጠሩ ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር የማዋል ሥራም እንዲሁ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
በክልሉ በየአካባቢው ህዝቦች የሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎች ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ አይገባም ያሉት አቶ ርስቱ እነዚህን አጀንዳዎች ተጠቅመው ክልሉን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል። ለዚህም የፀጥታ አካላት ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ አመራሩም በቁርጠኝነት መታገልና ህዝቡን የማንቃት ሥራ መስራት አለበት ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
- Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack… I am trying not to be an alarmist, but there are a lot of things that have happened over the last 16 months that I was previously led to believe would never happen. And the tension… Read more: Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
- U.S. Considers Somaliland Recognition in Exchange for Strategic Military Base Near BerberaAccording Financial Times a U.S. official, discussions have begun regarding a potential deal that would involve the United States recognizing Somaliland in exchange for establishing a military base near the strategic port of Berbera. This development, if confirmed,… Read more: U.S. Considers Somaliland Recognition in Exchange for Strategic Military Base Near Berbera
- Brigade Nhamedu’s forthcoming Addis Ababa ConferenceBy Beyene Gerezgher The Ethiopia branch of Brigade Nhamedu (also known as the Blue Revolution Movement) will host a vital conference in Addis Ababa on January 25, 2025. The event will bring together Brigade Nhamedu leaders and… Read more: Brigade Nhamedu’s forthcoming Addis Ababa Conference
- Eritrea Is the North Korea of Africa: America Must ActThe U.S. Department of the Treasury should also tighten sanctions on Eritrean banks, financial institutions, and money transfer agencies such as Himbol. That an Eritrean ambassador identified Himbol’s operation is significant; that the Eritrean government scrambled to… Read more: Eritrea Is the North Korea of Africa: America Must Act