“ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት ነው፤ በአሁኑ ወቅትም ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል” – ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን
“ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት ነው፤ በአሁኑ ወቅትም ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል” ሲል ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን ተናገረ ፡፡
ከዚህ አኳያ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ የሚገኘው እርዳታ ለህብረተሰቡ እየደረሰ አለመሆኑን የሚያነሱ ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ሃሳብ ተገቢ መሆኑንም ገልጿል፡፡
አሸባሪው ህወሃት ከምስረታው ጀምሮ በዜጎች ደምና ስቃይ በመነገድ የሚታወቅ ድርጅት ሲሆን፤ በ1977 ዓ.ም በትግራይ በተከሰተው ረሃብ የፈጸመው ዘግናኝ ድርጊት ደግሞ ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡
ቡድኑ ከደርግ መንግስት ጋር የትጥቅ ትግል እያደረገ በነበረበት በ1977 ዓ.ም በትግራይ እጅግ አስከፊ ረሃብ መከሰቱ ይታወሳል፡፡
ወትሮውንም ለህዝብ ደንታ የሌለው ይህ ቡድን በረሃብ የሚረግፉ ዜጎችን ሰቆቃ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከመላው ዓለም የተራድኦ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ተቋማት የሚቀርበውን እርዳታ ለመሳሪያ ግዥ ተጠቀመበት፡፡
በአንድ ወቅት የእንግሊዙ ታወቂ የቴሌቭዥን ጣቢያ (ቢቢሲ) ባሰራጨው መርማሪ ዘገባ ህወሃት በወቅቱ በእርዳታ ከሚቀርበው እህል ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ለህብረተሰቡ በማድረስ ቀሪውን ለመሳሪያ ግዥ ይጠቀምበት እንደነበር ከቡድኑ መስራቾች መካከል ዶክተር አረጋዊ በርሄን ጠቅሶ መዘገቡ አይዘነጋም፡፡
በዚህም በትግራይ በርካታ ዜጎች በረሃብና ቸነፈር ምክንያት ለሞት ተዳርገዋል፡፡
“ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ” እንዲሉ አሸባሪው ህወሃት አሁንም ወደ ትግራይ የሚገባውን እርዳታ ለጦርነት ዓላማ እየተጠቀመበት መሆኑን የሚያነሱ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ተበራክተዋል፡፡
ኒውዝላንዳዊው ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን ከኢዜአ ጋር በነበረው ቆይታ አሸባሪው ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት መሆኑን አንስቷል፡፡
የሽብር ቡድኑ በ19 80ዎቹ በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ረሃብ ተከትሎ ከዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች ይቀርብ የነበረውን ሰብዓዊ ድጋፍ ለጦር መሳሪያ ግዥ እንዳዋለው አስታውሷል።
ቡድኑ አሁንም ተመሳሳይ ድርጊት እንደሚፈጽም ነው ጋዜጠኛው የሚያብራራው፡፡
የሽብር ቡድኑ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ ክልል የገቡ ተሽከርካሪዎችን በማገት ለጦርነትና በወረራ ይዟቸው በነበሩ አካባቢዎች ንብረት ለመዝረፍ መጠቀሙንም ነው የገለጸው፡፡
ቡድኑ የእርዳታ መጋዝኖችን በመዝረፍ ጭምር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሃብትን ለጦርነት ማዋሉ ግልጽ ነው ሲል አብራርቷል፡፡
“የመንግስታቱ ድርጅት ይህን የቡድኑን ህገ-ወጥ አካሄድ በግልጽ ሲያወግዝ አይታይም፤ ይህም ተቀባይነት የሌለውና የዓለም አቀፍ መርሆችን የጣሰ አካሄድ ነው” ብሏል፡፡
ከዚህ አኳያ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ጉዳዩን በሚመለከት ጥያቄ ላላቸው አካላት ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባም ነው የተናገረው፡፡
ቡድኑ በተለይ በአፋር ክልል የእርዳታ መስመሮች ላይ ወረራ በመፈጸም ሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ እንዳይገባ ሲፈጽም የነበረውን ህገ-ወጥ ተግባር የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊገነዘብ እንደሚገባም ተናግሯል፡፡
በመሆኑም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወደ ትግራይ ክልል የሚላከውን ሰብዓዊ እርዳታ ለምን ዓላማ እየዋለ መሆኑን በአግባቡ ማጣራት እንደሚጠበቅበት ተናግሯል፡፡
በተያያዘ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከድርጅቱ መርህ ባፈነገጠ መልኩ በሰሜን ኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ጋዜጠኛው ተናግሯል፡፡
በመሆኑም የመንግስታቱ ድርጅት የዓለም የጤና ድርጅትን ጨምሮ በስሩ ያሉ ተቋማትን አሰራር መለስ ብሎ ሊመረምር ይገባል ነው ያለው፡፡
የዓለም የጤና ድርጅትን ዋና ዳይሬክተር እያከናወነ ያለው ተግባር ትክክል አለመሆኑ በግልጽ ሊነገረው እንደሚገባም ነው ያነሳው፡
ENA
- Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack… I am trying not to be an alarmist, but there are a lot of things that have happened over the last 16 months that I was previously led to believe would never happen. And the tension between Cairo and Jerusalem is quite real—these stories are not on the order of Mossad gum or Mossad sharks. Cook-Steve-foreign-policy-columnist4 By Steven… Read more: Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
- U.S. Considers Somaliland Recognition in Exchange for Strategic Military Base Near BerberaAccording Financial Times a U.S. official, discussions have begun regarding a potential deal that would involve the United States recognizing Somaliland in exchange for establishing a military base near the strategic port of Berbera. This development, if confirmed, could significantly reshape the geopolitical landscape of the Horn of Africa. ” A US official briefed on Washington’s initial contacts… Read more: U.S. Considers Somaliland Recognition in Exchange for Strategic Military Base Near Berbera
- Brigade Nhamedu’s forthcoming Addis Ababa ConferenceBy Beyene Gerezgher The Ethiopia branch of Brigade Nhamedu (also known as the Blue Revolution Movement) will host a vital conference in Addis Ababa on January 25, 2025. The event will bring together Brigade Nhamedu leaders and representatives from the U.K., Europe, Canada, Uganda, and other countries. It will provide a valuable opportunity to assess… Read more: Brigade Nhamedu’s forthcoming Addis Ababa Conference