– 240 ሺህ ሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ይወስዳሉ
በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል ንቅናቄ ሊካሄድ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2015 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል።
በሪፖርታቸው ትምህርት ቤቶችን በማሻሻል የመማር ማስተማር ሒደቱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን የማስተካከል ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
በመሆኑም በሚቀጥሉት ሁለት ወራት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብር የሚጠይቅ አገራዊ የሕዝብ ንቅናቄ የሚደረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ 47 ሺህ አጠቃላይ ትምህርት የሚሰጡ የትምህርት ተቋማት መኖራቸውን ጠቅሰው ያሉበትን ደረጃ በሚመለከት ቀደም ብሎ ጥናት መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም በርካታ ትምህርት ቤቶች የሚጠበቀውን ደረጃ የማያሟሉ መሆናቸው ተረጋግጧል ያሉት ሚኒስትሩ በተባበረ አቅም የትምህርት ቤቶቹን ደረጃ ማሻሻል ያስፈልጋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሟላት ሕብረተሰቡን በማስተባበር በተሰበሰው 11 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር 8 ሺህ 702 ትምህርት ቤቶች ተጠግነው አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉን ገልጸዋል።
ዘንድሮ 240 ሺህ ሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ይወስዳሉ ፡- ትምህርት ሚኒስቴር
240 ሺህ ለሚደርሱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በበይነ-መረብ የመውጫ ፈተና ለመሥጠት መዘጋጀቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት ÷ በ2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ኘሮግራም ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመሥጠት ብሉ -ኘሪንት ተዘጋጅቷል፡፡
የመውጫ ፈተና የክፍያ ተመን ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱንም ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት አብራርተዋል፡፡
የመውጫ ፈተና ስትራቴጂ ማስፈፀሚያ መመሪያ እና የድርጊት መርሐ-ግብር ዝግጅት መጠናቀቁንም ጠቁመዋል፡፡
በመውጫ ፈተና የሚካተቱ የትምህርት ዓይነቶች ተለይተው በቅድመ-ምረቃ በሚሰጡ በሁሉም የትምህርት መስኮች የፈተና ንድፍ ማሳያ መዘጋጀቱን ማስረዳታቸውን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
OBN
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።ከትግራይ ጊዜያዊ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ ስፔሻሊስት ስለነበርኩ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም ” – የራሱን… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ እያነጋገረ ነው። በቅርቡ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚንስትር ደኤታ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. Conflict, famine and a great-power competition are colliding in… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣ ቶትነሃም ቦዶን በድምሩ አራት ለአንድ አሸንፈው ነው ለፍሳሚ የበቁት።… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል