የህንድ ዋና ከተማ ኒው ደልሂ ከ10 ቀናት በኋላ የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባን ለማስተናገድ ጉባዔው በዝንጀሮዎች እንዳይረበሽ እየተዘጋጀች ነው።
ከተማዋ እንግዶቿን ለመቀበል እያደረገችው ባለው ሽር ጉድ ውስጥ ለአንድ ጉዳይ የተለየ ትኩረት ሰጥታለች፤ ዝንጀሮዎችን ከመሰብሰቢያ አዳራሽ የማራቅ ዘመቻ። በከተማዋ የተለያዩ አቅጣጫዎች አስፈሪ የዝንጀሮ ምስሎች እና ቅርጾችን እያስቀመጠች ሲሆን፥ የእንስሳት ድምጽን የሚያስመስሉ የሰለጠኑ ሰዎችንም ለማሰማራት አቅዳለች ተብሏል።
በኒው ደልሂ ከ20 ሺህ በላይ ዝንጀሮዎች እንዳሉና በየዓመቱ በአማካይ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች በዝንጀሮዎች እንደሚነከሱ የታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ዘገባ ያሳያል። “ላንገርስ” የሚሰኙት ጥቁር ፊትና ረጅም ጭራ ያላቸው ዝንጀሮዎች ባህሪያቸው ቁጡ እና ሃይለኛ ናቸው።
በባለሙያዎች ቁጥጥር ካልተደረገባቸውም ጉዳት እንደሚያደርሱ የህንድ የዱር እንስሳት ጥበቃ ተቋም ይገልጻል። እናም ኒው ደልሂ ከፈረንጆቹ መስከረም 8 እስከ 9/ 2023 የምታስተናግደው የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ በዝንጀሮዎች እንዳይታወክ ከ30 በላይ የሰለጠኑ ባለሙያዎች በየሆቴልና ስብሰባ አዳራሹ ተመድበው ይሰራሉ ተብሏል።
የዝንጀሮዎቹን ድምጽ የሚያስመስሉት ባለሙያዎች ዝንጀሮዎቹ እንግዶቹን እንዳይረብሹ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። ዝንጀሮዎቹ ምግብ ፍለጋ ወደ ስብሰባ አዳራሾች እና ሆቴሎች እንዳያንዣብቡም ከተማዋ በየሥፍራው የምግብ ማቅረቢያ እያዘጋጀች ነው ተብሏል።
ኒው ደልሂ በፈረንጆቹ 2014 የላንገርስ ድምጽ የሚያስመስሉና ወደ ፓርላማ እና ሌሎች ቢሮዎች እንዳይገቡ የሚያስፈራሩ 40 ባለሙያዎችን ቀጥራ ነበር። በ2010 የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች በከተማዋ ሲደረግም አትሌቶች በእነዚህ ዝንጀሮዎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው 38 የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ማሰማራቷን ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል።
በጋዜጣው ሪፖርተር
አዲስ ዘመን ነሃሴ 25/2015
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ