በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡
እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። ይህ ደግሞ በክልሉ ምጣኔ ሃብት ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ነው ቢሮው ያስገነዘበው።
የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ይሄነው ዓለም እንዳሉት ሰላም የሌለው ክልል አልሚዎችን ሊስብ አይችልም፡፡ አልሚዎች ለዳግም ኢንቨስትመንት በተለይም አዳዲስ ማሽኖችን ለማስገባት ያላቸውን ፍላጎት እንደሚቀንስም አብራርተዋል፡፡
ሰላም ከሌለ ኢንቨስትመንቱ አትራፊ ስለማይኾን አዳዲስ የሥራ እድል መፍጠር እንደሚሳነው እና ምርትም ማምረት እንደማይቻል አስገንዝበዋል፡፡
አሁን ላይ ያለው አለመረጋጋት የጥሬ እቃ ዝውውርን እየገታ በመኾኑ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት እንዳልተቻለ የሚናገሩት የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊው ጉዳዩ የውጭ ምንዛሬን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ይሄነው በሰላም መደፍረሱ ምክንያት ተጨማሪ ምርት አምርቶ በገበያው ላይ የሚታየውን የዋጋ መናር ለመቀነስ አስቸጋሪ እንዳደረገውም ነው ያስገነዘቡት፡፡
እየተፈጠረ ባለው ችግር ዋነኞቹ ተጠቂዎች ፋብሪካዎች ኾነዋል ፤ ይህም በፋብሪካዎቹ የሚሠሩ ሠራተኞችን ከሥራ እያፈናቀለ ስለመኾኑ ነው ያብራሩት፡፡ ባለፈው ጊዜ በተከሰተው አለመረጋጋት ብቻ ከ3 ሺህ በላይ የፋብሪካ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው ስለመፈናቀላቸው ነው የገለጹት፡፡
በተለይም እስከ 8 የሚጠጉ የእርሻ ኢንቨስትመንቶች ላይ ጉዳት በመድረሱም ክልሉ እየተጎዳ ስለመኾኑ ነው ያስገነዘቡት፡፡
ከዘጠኝ በላይ በሚኾኑ የአበባ ልማት ዘርፎች ላይ ጉዳት በመድረሱ በዓመት ከ9 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መታጣቱንም አብራርተዋል፡፡
የክልሉን ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በክልሉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እና አሁን የተጀመረውን አንጻራዊ ሰላም ለማስቀጠል የሁሉንም የክልሉን ሕዝብ ለሰላም መረባረብን ይጠይቃል። (አሚኮ)
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza,… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ