ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል። ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ። እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ጳግሜን 5 የትውልድ ቀን ” ኢትዮጵያ የትውልዶች ድምር” በሚል መሪ ሃሳብ በፌዴራል ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ፍትሕ ሚኒስቴር በጋራ ባዘጋጁት የትውልድ ቀን በዓል ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ አርበኞች፣ አረጋዊያን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለበዓሉ ታዳሚዎች መልእክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአሁኑ ትውልድ ካለፈው የሚማር እና ለሚመጣው የሚያስተምር መደላድል ነው ብለዋል፡፡ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ቆመን ያለፈውን እና የሚመጣውን ስናስብ ለነገ ተስፋ የምናይበት ነው ብለዋል፡፡
ሽግግሩ የአንድ ዓመት ብቻ ሳይኾን በርካታ ዘመናትን አስታውሰን፤ እልፍ ዘመናትን የምንቀበልበት ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ የእርሳቸው ትውልድ በርካታ ጥሩ ነገሮች እንዳሉት አንስተው አሁናዊው ትውልድ ሊማርበት የሚገባ በርካታ ጉድለቶች ነበሩበት ብለዋል፡፡ ሀገር ወዳድነት፣ ማንበብ፣ ማሰብና ማንሰላሰል እንዲሁም ምክንያታዊነት የዚያ ዘመን በጎ ጎኖች ነበሩ ብለዋል፡፡
“የእኛ ትውልድ የትግሉ ማዕከል ሀገሩ ነበረች” ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ነገር ግን ዓለምን የምንመለከትበት መነጽር ጠባብ በመኾኑ በርካታ ዋጋ ከፍለናል ብለዋል፡፡ አንድ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም እንደ መታገያ መስመር መውሰድ እና እርሱን ብቻ መፍትሔ አድርጎ መመልከት ድክመት ነበር፤ የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ አለማስገባትም ዋጋ አስከፍሏል ብለዋል፡፡
ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው ብለዋል፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ነው ያሉት፡፡
ሚኒስትሩ በንግግራቸው ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ትውልዱ የተወዛገበ የሞራል መሰረት ላይ መቆሙን ጠቁመው፤ “እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ብለዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ እየፈጸማቸው ያሉ የሥርዓተ-ትምህርት ማሻሻያ እና የትምህርት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ዓላማው ተማሪዎችን መጣል ሳይኾን ራሱን ችሎ የሚቆም ትውልድ ማፍራት እንደኾነ አንስተዋል፡፡
በጎ፣ ግብረ-ገብ፣ አንሰላሳይ፣ አሳቢ፣ ምክንያታዊ እና ትጉህ ተማሪ ለማፍራት ኢትዮጵያዊያን በጋራ እንዲቆሙም ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው አሚኮ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. Conflict,… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣ ቶትነሃም… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል