በግብጽ ካይሮ ሲካሔድ የቆየው ሶስተኛው ዙር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ ደንቦች እና መመሪያዎች የሶስትዮሽ ድርድር ተጠናቀቀ።
ለሁለት ቀናት በተካሔደው መድረክ የሶስቱ ሃገራት ተወካዮች ጠንካራ ድርድር ማድረጋቸው ተገልጿል።
በድርድሩ ላይ በኢትዮጵያ በኩል በሚኒስትር ማዕረግ ዋና ተደራዳሪ በአምባሳደር ስለሺ በቀለ ፣ በግብጽ በኩል የውሃ ሃብትና መስኖ ሚኒስትሩ በፕሮፌሰር ሃኒ ሰዊላም እንዲሁም በሱዳን በኩል በተጠባባቂ የመስኖና ውሃ ሃብት ሚኒስትር በዳወልበይት አብደልራህማን የተመሩ አባላት ተሳትፈዋል።
የሶስቱ ሃገራት ተደራዳሪዎች ወደጋራ መግባባት በሚያደርሱ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ተወያይተዋል።
በመጨረሻም ቀጣዩን ዙር ድርድር ለማካሔድም በፈረንጆቹ ወር ዲሴምበር 2023 አዲስ አበባ ላይ ለመገናኘት ተስማምተዋል።
ኢትዮጵያ በአባይ ውሃ አጠቃቀም ላይ ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ስምምነት ላይ ለመድረስ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል