ጆንሰን በቴሌቪዥን ጣቢያው የፕሮግራም አቅራቢ፣ አዘጋጅና ተንታኝ ይሆናሉ። በቀጣይ ዓመት የአሜሪካና የዩኬ ምርጫ በመዘገብ “ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ” ተብሏል። “የእንግሊዝን ኃይል የሚያሳይ መሰናዶ” ያቀርባሉም ብሏል ጂኒ ኒውስ። በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ምልከታቸውን ለማጋራት ቃል ገብተዋል።
በዴይሊ ሜይል ላይም አምደኛ የሆኑት ቦሪስ ጆንሰን ሥራቸውን በአውሮፓውያኑ አዲስ ዓመት ይጀምራሉ። ቦሪስ ጆንሰን በኤክስ ገጻቸው ላይ “ጂቢ ኒውስን እንደምቀላቀል ስነግራችሁ በደስታ ነው” ብለው ቪድዮ አጋርተዋል።
“በሩሲያ፣ ቻይና፣ ዩክሬንና ሌሎችም ጉዳዮች እውነተኛ ዕይታዬን አቀርባለሁ” ብለዋል። “እንግሊዝ በዓለም ስላላት ዕምቅ አቅምና ፈተናዎቻችንም እናገራለሁ” ሲሉ አክለዋል። ቦሪስ ከሥልጣን እንዲወርዱ ከፍተኛ ጫና መፈጠሩን ተከትሎ ነው አምና የወረዱት። በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ያሳዩት አመራር አሁንም ምርመራ እየተደረገበት ነው።
በዩኬ የቀድሞ መሪዎች ሥልጣን በለቀቁ በሁለት ዓመታት ስለሚይዙት ሥራ የሚያማክሩት አገራዊ ኮሚቴ አለ። ይህ ኮሚቴ ቦሪስ ጆንሰን ጂቢ ኒውስ መግባታቸው ከመንግሥት መርህ ጋር የሚጻረር ስላልሆነ ፈቅዷል። ሥልጣን ላይ ሳሉ ያገኟቸውን መረጃዎች ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ መርሆች ተቀምጠዋል። በተጨማሪም ጂቢ ኒውስን ወክለው መንግሥት ላይ ጫና እንዳያደርጉም ጥንቃቄ ይደረጋል።
ይህ የሚሆነው ሥልጣን ከለቀቁበት ጊዜ በኋላ ላሉት ሁለት ዓመታት ነው። ቦሪስ ከሥልጣን በለቀቁ በአምስት ወራት ውስጥ በተለያዩ መሰናዶዎች ንግግር በማድረግና የግል የሕይወት ታሪካቸውን ለመጻፍ በመስማማት አራት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ፓውንድ አግኝተዋል። ጂቢ ኒውስ ከዚህ በፊት ታዋቂው ኮሜድያን ጆን ክሊስን ቀጥሯል። ጣቢያው ቦሪስ ጆንሰንን ከቀጠረ በኋላ የተመልካቾቹ ቁጥር ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza,… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ