ዛሬ በተከበረው 119 የአገር መከላከያ ሰራዊት ቀን ላይ “ወረን አናውቅም፣ ወደፊትም ማንንም አንወርም” ሲሉ የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ተናገሩ። ዋና አዛዡ ይህን ያሉት ሰሞኑን ኢትዮጵያ ይፋ የባህር በር አስፈላጊነት ሳቢያ ከዚያም ከዚህም የጦርነት አሳብ እንዳለ አድርገው ለሚያስቡና ስጋት ለገባቸው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
መከላከያ በአዲስ መልኩ በልዩ ሪፎርም መደራጀቱን ያስታወቁት አብይ አህመድ ችግሮች በጠረጲዛ ዙሪያ ሊፈቱ እንደሚገባ አስታውቀዋል። ይህን ታላቅ ሰራዊት አዘምኖ በማደረጃቱ በኩል ሰፊ ድርሻ ላበረከቱ ታላቅ ምስጋና ያቀረቡት አብይ አህመድ ” ኢትዮጵያ ተሸንፋ አታውቅም፣ ወደፊትም አትሸነፍም። ታላቅ አገር ለልጆቻችን እናስረክባለን” ሲሉም ተሰምተዋል።
በሰራዊቱ ዘንዳ ትልቅ አክብሮትና ፍቅር እንዳላቸው የሚነገርላቸው አብይ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አሁን ካለው በላይ እንደሚያዘምኑት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ የማይለው የአገር መከላከያ ሃይል ኢትዮጵያን በአስተማማኝ ደረጃ እንደሚተብቅና ለማናቸውም ዓይነት ጠላት ግብረ መልስ እንዲሰጥ ተደርጎ መገንባቱን ” ሁሉም ይስማ” በሚል መልኩ ገልጸውል። ይህን ሲሉ የአገር መከላከያ ለቀጠናውና ለአፍሪካ እንደተለመደው አለኝታነቱን እንደሚያሳይ ደጋግመው ታሪክ በማጣቀስ ማስገንዘቢያ በመስጠት ነው።
በዚሁ “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” በሚል መሪ ሃሳብ ነው በተከበረው የአገር መከላከያ ቀን በዓል ። የጦር ኀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ መከላከያ ማለት ማንዴላን ያሠለጠነ፣ ሙጋቤን ያስደመመ፣ ከሱዳን እስከ ሊቢያ፣ ከኩባ እስከ ላይቤሪያ በመከራ ተፈትኖ በድል የጸና ሠራዊት ማለት ነው ብለዋል፡፡
ጠቅላይ አዛዡ በንግግራቸው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት በጦር ሜዳ ከሚያስመዘግበው ጀግንነት በላይ የኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊያን የሰላም አምባሳደር ነው ብለዋል፡፡ ሰላም አስከባሪ የኾነው ሠራዊት አጥንቱን የሚከሰክሰው ደሙንም የሚያፈሰው በሦስት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ነው ያሉት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ያለንን ሰላም ለማጽናት፣ የጠፋ ሰላምን ለመመለስ እና የመጣ ሰላምን ለማጽናት ውድ የሚባል ዋጋ ይከፍላል ብለዋል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር የሚከተለውን መግለጫ አሰራጭቷል።
“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት ” በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን ።
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት።
ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል።
በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ በሠራዊቷ ኮርታ እንጅ አንድም ጊዜ አፍራ እንደማታውቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው ።
ዛሬ ላይም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ሀገረ ጠል በሆኑ ባንዳዎችና የፀረ ሠላም ሀይሎች ችግሮች ቢከሠቱም ጀግንነት ባህል ልምዱ እና የዘወትር ተግባሩ ባደረገው ሠራዊታችንና ህዝባችን የሠላም እንቅፋቶችን ፈተና ተቋቁማ ሀገራችን በልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች።
በመሆኑም በየትኛውም ጊዜ እና በማንኛውም ቦታ ለሠራዊታችን ብርታት ሞራልና የጀርባ አጥንት ከሆነው ህዝባችን ጋር ሆነን ሠላማችንን እያሥቀጠልን እንገኛለን።
116ኛው የመከላከያ ሠራዊት ቀንም ይበልጥ ቃላችንን የምናደስበት በየዘመናቱ ለሀገራችን ሉዓላዊነት ሲሉ መስዋዕት የከፈሉ ጀግኖችን የምንዘክርበትና ከመላው ህዝባችን ጋር ሆነን ለሀገራችን ሠላምና ልማት ማበብ በጋራ የምንቆምበት ዕለት ጭምር ነው።
እናም እንደ መሪ ቃላችን በተፈተን ጊዜ ሁሉ ፀንተን የድል ሠራዊት ሆነን ዛሬ ላይ እንደደረሥነው ቀጣይም ከመላው ህዝባችን ጋር ለሀገራችን መክፈል ያለብንን ሁሉ ዋጋ በመክፈል የኢትዮጵያን ሠላም እና ዕድገት አፅንተን እናሥቀጥላለን ።
“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ