በሃይማኖታዊ እና ሕዝባዊ በዓላት፤ በብልጽግና ፓርቲ ሥልጠና የክልሉ ሕዝብ ላሳየው ፍቅር፣ ትብብር እና የጋራ ኀላፊነት ስሜት የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ምሥጋና ካቀረበ በሁዋላ ነው የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ የሰዓት ማሻሻያውን ያስታወቀው።
” ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ከበባ ውስጥ እንደምትገኝ ህዝባዊ ሃይሉ አስታውቋል።ከተማዋን በቀላሉ ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ሁኔታዎች በመኖራቸው …” በሚል ምናላቸው ስማቸው የንቅናቄውን አመራሮች ዋቢ አድርጎ አስጠንቅቆ ነበር። መንግስትም ተስፋ መቁረጡን፣ እንዲሁም 23ኛ ክፈለጦር ሙሉ በሙሉ መደምሠሱንም ምናላቸው ስማቸው በህዝብ ግንኙነት ደረጃ አስታውቆ ነበር።
ሌላው የህዝብ ግንኙነት ዓይነት መረጃ የሚሰጠው ደረጀ ከባህር ዳር ከአንድ የንቅናቄው የጦር አመራር ጋር በቀጥታ ስርጭት ባደረገው ውይይት መሳሪያ መጨረሳቸውን፣ ተጨማሪ ፋኖ የመጣል ቢባልም እንዳልደረሰ፣ ዘመነ ካሴ አለ በሚባልበት (አዴት ግድም ነው) መንግስት የከፋ ድብደባ መፈጸሙ፣ በቋሪት አቅጣጫም ሃይል አጠንክሮ በከባድ መሳሪያ እያጠቃ መሆኑን ተናጋሪው ካስታወቀ በሁዋላ ” በግለሰቦች ቤት መሳሪያ ያለው ሁሉ መሞቱ ስለማይቀር እንዲዋጋ ቢደረግ” ሲል ተደምጧል። መረጃው አሜሪካ ያለው ምናላቸው በቋሪት በኩል የመከላከያ ሃይል እየተደመሰሰ ነው ካለው መረጃ ጋር የሚቃረን በመሆኑ ደረጄ ” መረጃው የተለይ ሆኖብኛል” ለማለት ሲገደድ ለመስማት ተችሏል።
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ በክልሉ በርካታ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም መደፍረስ ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን አስታውሶ፣ ጥቅምት 10/2016 ዓ.ም የክልሉን ወቅታዊ የሰላም ኹኔታ በጥልቅ የገመገመው የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ነው ያመለከተው።
የአማራ ክልል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኅላፊ እና የኮማንድ ፖስቱ አባል መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) በሰጡት መግለጫ የሰዓት እላፊ ገደብ ማሻሻያው እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ኹኔታ የሚወሰን ይኾናል ብለዋል። ይህንን ተከትሎም በጎንደር እና ደብረ ብርሃን የተሽከርካሪ ስዓት እላፊ ገደብ ባለበት የሚጸና ኾኖ ለሰው እስከ ምሽቱ 3:00 ሰዓት መንቀሳቀስ የሚያስችል ማሻሻያ ተደርጓል።
ባሕር ዳር ከተማ ተሽከርካሪ እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት እና ለሰው እስከ 3: 00 ሰዓት ድረስ መሻሻሉን ዶክተር መንገሻ ጠቁመዋል። ዶክተር መንገሻ በመግለጫቸው በክልሉ በርካታ ከተሞች እየታየ ባለው የህዝብ ድጋፍና የጸጥታ መሻሻል ወደፊትም ተመሳሳይ የሰዓት ማሻሻያ ሊደረግ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል።
ከጦርነት ያላገገመው የአማራ ክልል በሚቻለው ሁሉ ሰላም እንዲወርድ ጠብመንጃ ያነሱ ወገኖች ሁሉ ወደ ድርድር እንዲያመሩ አቅሙ ያላቸው በሙሉ ሊሰሩ እንደሚገባ፣ ውጭ ተቀምጠው ጦርነት የሚቆሰቁሱና ንግድ የሚያጧጡፉ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ህዝብ ጫና እንዲያደርግ በርካቶች እየጠየቁ ነው። የአማራ ክልል ጦርነት ለዩቲዩብ ነጋዴዎች ሲሳይ የሆነ ሲሆን፣ ለጦርነቱ ምዋጮ እንሰበስባለን የሚሉና ” ሚዲያዬን፣ አገልግሎቴን እርዱ” በሚሉ የደም ነጋዴዎች ኪስ ማደለቢያ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። እነዚህ ወገኖች ብህዝብ ደም፣ እልቂትና መፈናቀል ንግድ በመስከራቸው ጦርነቱ እንዲቆምና ንግግር እንዲጀመር የሚሰሩ አካላት ላይ የተባበረ ክንዳቸውን እንደሚያሳርፉ፣ ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ ሳይቀር የማቆሸሽ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ በተደጋጋሚ የታየ ሃቅ ነው። እነዚህ ወገኖች “ግፋ በለው” አቁመው መንግስትም ሆነ ታጣቂዎች ወደ ሰላም እንዲያመሩ ጫና ቢፈጥሩ ንግዱ ስለሚቆምባቸው አያስቡትም ሲሉ በደንብ የሚያውቋቸው ይገልሳሉ። ሰሞኑንንበገንዘብ የተነሳው ጸብም የዚሁ ማሳያ እንደሆነ ያመልክታሉ።
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments in Syria, and… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ ሳይንስን… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ