በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በአገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጠበቃ ነኝ በማለት በርካታ ክሶችን ተከራክሮ የረታው ግለሰብ በባለሥልጣናት በቁጥጥር ስር ዋለ።
ግለሰቡን በተመለከተ የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት “ጠበቃው” ከመታሰሩ በፊት ከከፍተኛው ፍርድ ቤት ጀምሮ አስከ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ድረስ 26 ጉዳዮችን ይዞ በመከራከር ለመርታት ችሏል።
ግለሰቡ ሊያዝ የቻለው ለኬንያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ተገቢው ትምህርት እና ብቃት ሳይኖረው በማስመሰል በዘርፉ በመሰማራቱ ከተለያዩ ሰዎች ጥቆማ ከደረሰው በኋላ ነው።
የሕግ ባለሙያዎቹ ማኅበር በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው ግለሰቡ፣ ጠበቃ እንዳልሆነ እና በኬንያ ውስጥ በጠበቅና እንዲሠራ የሚያስችለው ፈቃድ የሌለው ነው።
“ግለሰቡ በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጠበቃ እንደሆነ እና የማኅበሩ አባል መሆኑን በመግለጽ ሲያጭበረብር ነበር” ሲል ማኅበሩ ከሷል።
የሕግ ባለሥልጣናት ጨምረውም ግለሰቡ ተገቢው ትምህርት እና ፈቃድ ሳይኖረው ለምን ያህል ጊዜ በጥብቅና እንደሠራ ባይገለጹም በርካታ ጉዳዮችን ለማሸነፍ መብቃቱ ተነግሯል።
ብሪያን ምዌንዳ በሚል ስም የሚታወቀው ይህ ግለሰብ ከዚህ ቀደም በአገሪቱ ውስጥ አሳሳቢ ሆኖ የነበረው “ሙንጊኪ” የተባለው የወንጀል ቡድን መሪን በመወከል በቴሌቪዥን በተለላፈ የፍርድ ሂደት ላይ ተሳትፎ እንደነበር ይነገራል።
ግለሰቡ ሐሰተኛ መሆኑ ከተነገረ በኋላም በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይኽው ቪዲዮ በስፋት እየተዘዋወረ ይገኛል።
የኬንያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ግለሰቡ ተመሳሳይ ስም ያለውን ሕጋዊ ጠበቃ ግለ ታሪክ ከማኅበሩ ድረ ገጽ ላይ በመውሰድ እርሱን መስሎ ሲያጭበረብር ቆይቷል ብሏል። BBC
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. Conflict,… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣ ቶትነሃም… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል