በወለጋ የተለያዩ ግንባሮች የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መሪ ናቸው የተባሉትን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ይፋ ያልሆነ ታጣቂዎች መማረካቸው ተሰማ። በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው መመለሳቸውን ተቤኒሻንጉል ክልል ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ምስልና ቪዲዮ አስደግፎ አስታወቀ።
በዳሬ ሰላም የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራሮች ጋር ንግግር እየተደረገ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ኦፕሬሽኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ያስታወቁት ክፍሎሽ እንዳሉት በሰሙሉ ወጊያ በተለይም ከትናንት በስቲያ የኦነግ ሸኔ አዋጊዎች ናቸው የተባሉ መማረካቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የትጥቅ ትግል በሚያደርጉት የተለያዩ ስያሜ ያላቸው ላይ ታቂዎች ላይ በተመሳሳይ ሙሉ ማጥቃትና ማጽዳት መጀመሩ ይፋ በተነገረበት ወቅት፣ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሰፊ ይዞታቸውን እያጡና እየተማረኩ መሆናቸው መንግስት በይፋ ባይገልጽም በአካባቢው ያሉ ምስክሮች አረጋግጠዋል።
“በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጠቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም ተመልሰዋል” ሲል ነው ቢሮው ይፋ ያደረገው።
በመኩሪያው ዚፋሃ እና በመኮነን ፋኖ በሚባሉ ግለሰቦች ሲመራ የነበረው የጉህዴን ታጣቂዎች ቡድን በውይይት የሰላም ስምምነት መቀበሉ ታውቋል። ውይይቱ ሰፊና ከፍተኛ ጥረት የተደረገበት እንደሆነ ተመልክቷል።
በማንዱራ ወረዳ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲገቡ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና የሀገር ሽማግሌዎች በገነተ ማሪያም ከተማ በመገኝት አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ፣ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመቀበል ወደ ህብረተሰቡ መመለሳቸው የቀጠናውን ሰላም በዘላቂነት የተረጋጋ እንዲሆን ያደርገዋል ብለዋል።
ተመላሾችን በተማሩበትና ፍላጎታቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት በተለያዩ የግብርና ዘርፎች ለማሰማራት እንደሚሠራም ተናግረዋል።
በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ጫካ ውስጥ መቀመጫቸውን አድርገው በአዋሳኝ አካባቢዎች ስጋት ሲፈጥሩ የነበሩ ታጣቂዎች በውይይት መምጣቸው ለህብረተሰቡ ሰላም ዘላቂ መፍትሄ እንደሚሰጥም ነው የተገለጸው።
የሰላም ስምምነቱን ተግባረዊ ለማድረግና ወደ ሰላምና ልማት ለመግባት የሀገር ሽማግሌዎችና አመራሮች በተገኙበት ከሰላም ተመላሾች ጋር በጉሙዝ ብሄረሰብ ባህል መሠረት የእርቅ ስነ ስርዓት መካሄዱን የመተከል ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ ያመለክታል።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።ከትግራይ ጊዜያዊ መንበራቸው በአመጽና በጠመንጃ ኃይል እንዲወገዱ የተደረጉት አቶ ጌታቸው ውስን ያሉዋቸውን ጄነራሎች ስም እየጠቀሱና በጥቅሉ ተጋባራቸው “የብረሃን ስራ በብርሃን ነው” እንደተባሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ ስፔሻሊስት ስለነበርኩ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም ” – የራሱን ሰርግ አቋርጦ ቀዶ ሕክምና በማድረግ ሕይወት የታደገዉ ዶክተር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሌ ከተማ አስተዳደር የበሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ እያነጋገረ ነው። በቅርቡ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚንስትር ደኤታ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት በ “X” ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ቡድን ተቸካይ ነው። የትህነግ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. Conflict, famine and a great-power competition are colliding in the Horn of Africa, creating enormous instability. The growing prospect of overlapping civil wars and conflicts between nations in the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣ ቶትነሃም ቦዶን በድምሩ አራት ለአንድ አሸንፈው ነው ለፍሳሚ የበቁት። ለበርካታ ድል ሲተበቅ የነበረው አርሰናል በጉዳት ሳቢያ ቢንሸራተትም ከሁሉም ውድድር መውጣቱ ደጋፊዎቹን አበሳጭቷል። በፕሪምየር ሊጉ ታች የሚዳክሩት ሁለቱ ክለቦች ለፍጻሜ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል