የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ አንድ ሺህ አንድ መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ያወጣውን ማስታወቂያ ተከትሎ ተመዝጋቢ ስራ ፈላጊ ሃኪሞች ባለማግኘቱ በጀቱን ማዛወሩን አስታወቀ። ሃኪሞች ከተመረቁ በሁዋላ ስራ ማጣታቸው በተደጋጋሚ የሚገለጸውን ሮሮ እንደነበር ይታወሳል።
“ቢሮው ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ ማዛወሩን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል” ሲል ገጹ እንዳስታወቀው ክልሉ የሃኪሞች እጥረት እንዳለበት ሃላፊው አስታውቀዋል።
የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ቢያስታውቁም አሁንም ከተገኘ ሃኪም መቅጠር እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በምን ምክንያት ገበያው ላይ ሃኪም ማግኘት እንዳልተቻለ አላብራሩም። “ለሁለት ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም” ከማለት ውጭ ዝርዝር አላቀረቡም።
በክልሉ በተያዘው አሰራር በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር አለባቸው። በዚሁ መሰረት በገጠር ጤና ተቋማት ሃኪሞችን መድቦ ለማሰራት ማስታወቂያ ቢወጣም ሀኪሞችን ማግኘት አልተቻለም። በዚህም ሳቢያ በምትኩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር መገደዳቸውን ሃላፊው ገልጸዋል፡፡
“ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር” ያሉት ሃላፊዉ አሁን ላይ ቁጥሩ ወደ 85ሺህ ከፍ ማለቱን ግልጸዋል፡፡
“በተቻለን አቅም ማስታወቂያ አዉጥተን ገበያ ላይ የነበሩትን ለመዉሰድ ሞክረናል። ነገር ግን አሁንም የሀኪሞች ዕጥረት አለብን” ያሉት ሃላፊው፣ “ማስታወቂያዉን አይተዉ የመጡትን እንቀጥራለን ፤ካልመጡ ግን ገበያዉ ላይ የሰዉ ሃይል እንደሌለ ነዉ የሚቆጠረዉ” ብለዋል። ይህ ንግግራቸው “ተመርቀው ስራ አላገኙም፣ አይ ይህቺ አገር” በሚል ሲወቅሱና ሲያማርሩ የነበሩ አካላትን መረጃ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ሆኗል።
ሃላፊዉ በተጨማሪም ባለፈዉ ዓመት ሃኪሞችን ለመቅጠር ባወጣነዉ ማስታወቂያ ሀኪሞችን ማግኘት ስላልቻልን ወደ 7 መቶ አከባቢ የሚሆኑ የተለያዩ ባለሙያዎችን ቀጥረናል ሲሉም ነግረዉናል፡፡
ከኦርሚያ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ አካባቢ አስተዳእሮች እንደሚሰማው ሃኪሞች ገጠር ገብተው ማገልገል አይፈልጉም። ምንም የሰላም ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች እንኳን ቢሆን ለተወሰነ ጊዜ ገጠር ገብተው ያስተማራቸውን ህዝብ የማግለገል ተነሳሽነት የላቸውም። እርግጥ አስፈጊ የመኖሪያ ሁኔታዎች መሟላት እንዳለባቸው ቢታመንም “ገጠር ግብቶ የመስራት ፍላጎት ማጣት በአገር ደረጃ መነጋገሪይ፣ በማህበራቸው ዘንዳም አጀንዳ ሊሆን ይገባል” የሚሉ አሉ።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል።… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል