የትህግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ በለኮሰው ጦርነት እጅግ አስቸጋሪ ዓመታትን ያሳለፉት የትግራይ ተማሪዎች በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 69.9 በመቶ የሚሆኑት ማለፋቸው ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ዜናው መነጋገሪያ ሆኗል።
ትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 69 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆኑት 50 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው መነጋገሪያ የሆነው በሌሎች ሰላም ባለባቸው አካባባኢዎችና ክልሎች የሚኖሩ ተማሪዎች ያላገኙት ውጤት በትግራይ መመዝገቡ ነው።
ከፍተኛ አድናቆት የተሰጣቸው የትግራይ ክልል ተማሪዎች ፈተናውን ያለፉት ቀደም ሲል በክልሉ በወጉ የተዘረጋው የትምህርት አሰጣጥ ጥሩ መሰረት የጣለ እንደሆነ አንዳንዶች በማህበራዊ ገጾቻቸው እየገለጹ ነው። ያም ሆነ ይህ ትግራይ ካስለፈችው የጦርነት ዓመታት በመውጣት በአጭር ጊዜ የተማሪዎች ዝግጅት ይህ ውጤት መመዘገቡ በርካታ የጥናት መነሻ ሊሆን እንደሚችልም እየተጠቆመ ነው።
በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር ዓቀፍ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 69 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆኑት 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከመግለጹ ውጪ ስለተማሪዎቹ ትጋትና ልዩ ውጤት ያስታወቀው ነገር የለም።
የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ በክልሉ ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር ዓቀፍ የፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን አስታውሰዋል።
በዚህም መሠረት ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 69 ነጥብ 96 በመቶ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጸዋል።
ከተመዘገበው ውጤት 657 ከፍተኛው ነጥብ መሆኑንም አመልክተዋል።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።ከትግራይ ጊዜያዊ መንበራቸው በአመጽና በጠመንጃ ኃይል እንዲወገዱ የተደረጉት አቶ ጌታቸው ውስን ያሉዋቸውን ጄነራሎች ስም እየጠቀሱና በጥቅሉ ተጋባራቸው “የብረሃን ስራ በብርሃን ነው” እንደተባሉ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ ብቻ ሳይሆን ለአከባቢውም ብቸኛ ስፔሻሊስት ስለነበርኩ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም ” – የራሱን ሰርግ አቋርጦ ቀዶ ሕክምና በማድረግ ሕይወት የታደገዉ ዶክተር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሌ ከተማ አስተዳደር የበሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት መመሰረቱ ተገለጸ። መሪ አለመሰየሙ እያነጋገረ ነው። በቅርቡ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚንስትር ደኤታ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት በ “X” ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ቡድን ተቸካይ ነው። የትህነግ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International Studies in Washington. Conflict, famine and a great-power competition are colliding in the Horn of Africa, creating enormous instability. The growing prospect of overlapping civil wars and conflicts between nations in the… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል። ማንችስተር አትሌቲክን በድምሩ ሰባት ለአንድ፣ ቶትነሃም ቦዶን በድምሩ አራት ለአንድ አሸንፈው ነው ለፍሳሚ የበቁት። ለበርካታ ድል ሲተበቅ የነበረው አርሰናል በጉዳት ሳቢያ ቢንሸራተትም ከሁሉም ውድድር መውጣቱ ደጋፊዎቹን አበሳጭቷል። በፕሪምየር ሊጉ ታች የሚዳክሩት ሁለቱ ክለቦች ለፍጻሜ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል