ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይፋ መሆን የጀመሩ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ” እውን እስካሁን የት ነበርን” የሚያሰኝ እንደሆነ በየአቅጣጫው ቀና ልቡና ካላቸው ወገኖች የሚሰማ ድምጽ ነው። ሰላም ቢሰፍንና አገሪቱ ከሴራ ፖለቲካ ብትፈወስ ምን ሊታይ እንደሚችልም ምኞታቸውን የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። ” ምን ዋጋ አለው?” በሚል የሚያጣጥሉም አሉ።

መልካም ጉዳይን አበረታቶ የጎደለውን በመጠቆም፣ ክፉውን ተግባር የሚተች የተቃውሞ አውድ ወይም የተቃዋሚ ድርጅት ባለመኖሩ፣ በአብዛኛው ሚዲያዎችም ከሟርትና ከአስደንጋጭ ዜና አዙሪት ለመላቀቅ አለመፈለጋቸው፣ ቢፈልጉም ላይክና ሼር ስለሚጉዝደል ጉሮሮ ስለሚዘጋ፣ አብዛናው የማህበራዊ ሚዲያም ተሰበረ፣ ወደመ፣ ተደመሰሰ፣ ፈረሰ፣ ተገደለ፣ ተማረከ ወዘተ ከሚሉ ዜናዎች ውጭ ስሜት ስለማይሰጠው በኤትዮጵያ ነገሮች ሁሉ ግራ የሚያጋቡ እንደሆኑ በዚሁ ችግር ዙሪያ ጥናት ያካሄዱ፣ የታዘቡ ይገልጻሉ።

በተለያ በአብዛኛው ሊባል በሚችል ደረጃ የሚዲያ ዘርፉ ቁልቁል ሄዶ መከስከሱ፣ የፖለቲካ አጀንዳ አራጋቢ መሆኑና በተወሰኑ ሃይሎች የሚደጎም መሆኑ የኢትዮጵያን ፖለቲካ አታካች አድርጎታል። ዓላማው ህዝብ እንዲሰላችና ዘወትር ምሬት ውስጥ እንዲወድቅ በመሆኑ፣ ከመንግስት ድክመት ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያን እጅግ እየጎዳት ነው።
“የአባይ ግድብ ተሸጠ” በሚል “የውስጥ አዋቂዎች ነገሩኝ” የሚል ተከፋይ ሚዲያ፣ ግድቡ እንደተባለው አለመሸጡ፣ ይልቁንም ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ኤለኤክትሪክ ለማምረት ከጫፍ መድረሱ በውል እየታየ ይቅርታ አይጠይቅም። ይህንኑ ልዩ ተልዕኮ ያለው ዜና በጅምላ ያሰራጩ በተመሳሳይ እርምት አይወስዱም። ከሁሉም በላይ ትልልቅ የሚባሉትን ጨምሮ ተከፋዮቹ ሚዲያዎች ሆን ብለው በተደጋጋሚ ስህተት ሲያትሙና ሲያሰራጩ በውል እየታየ አንባቢ፣ ተከታይ፣ አከፋፋይ “ውሸታም” ብሎ ሲቃወምና ጥንቃቄ ሲወስድ አይታይም። የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክን ጭምሮ የጫካ ፕሮጀክትና መላው የገበታ ለአገር ፕሮጀክቶች ላይ የተረጨው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ እንደሚለው ሳይሆን ውጤቱ ሌላ ነው።
የውድቀትና የክስረት ዜና ሲረጭበት የነበረው የጨበራ ጩርጩራ ፕሮጀክት ይህን ይመስላል
የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኮንታና በዳውሮ ዞኖች መካከል የሚገኝ ሲሆን ካለው ዕምቅ ከተፈጥሮ ሀብት አንፃር በቀዳሚነት ስሙ ይነሳል፡፡
ብሔራዊ ፓርኩ በ1997 ዓ.ም በኮንታና በዳውሮ ህዝቦችና አስተዳደር አካላት ጥያቄና ተሳትፎ መሰረት በብሔራዊ ፓርክ ደረጃ የተቋቋመ ሲሆን ፓርኩ የሚያካልለው የቆዳ ስፋት 1410 ካሬ ኪሎ ሜትር ስኩዌር ሲሆን በመካከለኛው ኦሞ ሸለቆ ውስጥም ይገኛል፡፡
ብሔራዊ ፓርኩ ከመዲናችን አዲስ አበባ በ475 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
ፓርኩ የግዙፉ የአፍሪካ ዝሆን መኖሪያ ሲሆን በውስጡ ከ800 በላይ የሚሆኑ ዝሆኖችና ከ 5 ሺሕ በላይ ጎሾች የሚገኙበት መሆኑ ፓርኩን ልዩ ያደርገዋል፡፡

በተጨማሪም 40 ትላልቅና መካከለኛ አጥቢ እንዲሁም 18 ትናንሽ አጥቢ የዱር እንስሳት ዝሪያዎች በውስጡ ይገኛሉ።
በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እንደ አጥቢዎቹ ሁሉ የበርካታ አዕዋፋት ዝርያዎች መኖሪያም ጭምር ነው፡፡ እስካሁን በተጠናው ጥናት 137 የአዕዋፍ ዝርያዎች የተለዩ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 6ቱ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፡፡
ፓርኩ በብዙ መልኩ የተፈጥሮ ሀብቱ የተጠበቀ ፓርክ ነው ያስባለው የእጽዋት ስብጥሩ እና ደኑ ነው። 106 እንጨታማ የእጽዋት ዝሪያዎች የሚገኝበት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ስድስቱ የእጽዋት ዝርያዎች በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፤ በተጨማሪም በውስጡ ከሚገኙ የዱር ዕፅዋት ዝሪያዎች መካከል ዝንጅብል፣ ቡና፣ ኮረሪማ፣ እንሰት፣ እጣንና የጌሾ ዝርያዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
በፓርኩ ውስጥ ብቻ 6 ሀይቆች የሚገኙ ሲሆን ባሄ፣ ቡሎ፣ ሺታ፣ ቆቃ፣ ከሪቤላና ጮፎሬ እጅግ አስደናቂና ሊጎበኙ የሚገቡ በብሔራዊ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ሐይቆች ናቸው፡፡
በብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ከሚገኙ ሐይቆች በአንዱ ብርቅዬ ወርቃማ የዓሳ ዝርያ የተገኘ ሲሆን በዓለም ሊቃውንት እውቅና አግኝቶ በሳይንሳዊ ስሙ ጋራ ጨበራ በመባልም ይጠራል፡፡
ሌላኛው ከብሔራዊ ፓርኩ ገፀበረከቶች መካከል ለአብነት ፏፏቴዎች፣ ፍልውሃዎችና የማዕድን ውሃዎች የሚጠቀሱ ናቸው።
ብሔራዊ ፓርኩ በአሁኑ ሰዓት በገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት እየለማ የሚገኝ ሲሆን ቱሪስቶች ብዙም ሳይጉላሉና ሳይለፉ በቀላሉ ጎብኝተው እንድመለሱ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም ባለፈ ፓርኩን በተገቢው ሁኔታ ለማስተዳደርና የዱር እንስሳትን በቅርበት ለመከታተልና ለመጠበቅ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
ይህ ብሔራዊ ፓርክ በኮንታ እና በዳውሮ ህዝብ ፊላጎት እንደተቋቋመ ሁሉ በጥበቃ ሂደት ላይም ህዝቡ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ብሔራዊ ፓርኩን ከተለያዩ ጥፋቶች በመታደግ መልካም ዝና እንድኖረው አድርገውታል።
ምንጭ ፦ የክልሉ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
- Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on EgyptIt was striking that, at the height of Israeli diplomacy’s preoccupation with tracking the repercussions of the aggression on Gaza, developments… Read more: Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ