“የህግ የበላይነት ለማስከበር እየተወሰደ ያለዉን እርምጃ መቋቋም የተሳናቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪዉ ሸኔ አባላት ለመንግስት እጅ ሰጡ” ሲል የዘገቡት መገናኛዎች እንዳሉት ድርጅቱ ቁመናው ፈርሷል።
በቅርቡ በታንዛንያ ለስምምነት ብዙ ርቀት ከተኬደና ከንግገሩ መልካም ዜና የተጠበቀ ባለበት ወቅት ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሰላም ንግግሩ የተኩስ ማቆም ስምምነት ተደርሶ እንደነበር፣ አነጋጋሪ የነበረው የስምምነቱ ቴክኒካል አፈጻጸም ጉዳይና ታጣቂዎችን አስመልክቶ እንዴት ይስተናገድ የሚል እንደነበር ውይይቱን የሚከታተሉ አስታውቀው መግለጻችን ይታወሳል።
በሁሉም ረገድ እጅግ ተስፋ ሰጪ ስምምነት ላይ እየተደረሰ ቆይቶ በመጨርሻው ቀን ሙሉ የአቋም ለውጥ በማድረግ ከአመክንዮ ውጭ የሆነ ጥያቄዎችን በማቅረቡ ውይይቱ መጨናገፉ ይፋ ቢሆንም፣ ቀጣይ ንግግር እንደሚኖር ተጠቁሞም ነበር።
በታንዛንያ ንግግሩ እየተደረግ ባለበት ወቅትም ቢሆን ወታደራዊ ኦፕሬሽኑን ያላቋረጠው መንግስት በተለያዩ ቀናት ኦነግ ሸኔ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገደና ታጣቂዎቹ በተለያየ መጠን እጅ መስጠታቸው ሲገለጽ ስንብቷል። ብዙ ባይባልም መሳሪያ መማረኩንም በምስል የሚያሳዩ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
ዛሬ ኦቢኤን እንዳለው ከሆነ በሺህ የሚቆጠሩ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ሰጥተዋል። እጃቸውን የሰጡት መከላከያ የሚያሳርፈውን ድብደባ መቋቋምና መመከት ባለማቻላቸው ነው።
“የተወሰደባቸዉን እርምጃ መቋቋም ተስኗቸዉ የተማረኩት ታጣቂዎች እንደ ተናገሩት ሸኔ ክፉኛ ተመትቶ በመፍረስ ላይ ይገኛል:” ያለው ሚዲያው “የሸኔ ኃይል በዉስጡ በተፈጠረዉ መከፋፈል እርስ በራሱ ወደ መጠፋፋት የተሻገረ በመሆኑ ለመንግስት እጅ ሰጥተናል” ሲሉ ታጣቂዎቹ ተስፋ መቁረጣቸውን አስታውቋል።
“ሸኔ የፍትህና የህዝብ ጥቅም ጠላት በመሆኑ እየፈረሰ ነው” ሲሉ እነዚህ የተማረኩትና በሰላም እጃቸዉን ለመንግስት የሰጡ የሸኔ ታጣቂዎች መናገራቸውን ዘገባው አክሎ ገልጿል። ይህን አስመልክቶ ኦነግ ሸኔ ይህ እስከታተመ ድረስ ማስተባበያ አልሰጠም።
- የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራኢትዮጵያ ከጅቡቲ ማግኘት የነበረባትን የባህር በር ሳታገኝ እንዲሁም በተመሳሳይ ኤርትራ ስትሄድ ለመውጪያም ሆነ ለመግቢያ ይጠቅማት የነበረን የባህር በር ሳታገኝ መቅረቷ ልብ ያደማል። የፖለቲካ… Read more: የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡ ” ለሆስፒታሉ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን መርጦ ድርጅት… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic and International… Read more: The Wars We Still Can Stop