ኢትዮጵያ አጠቃላይ ካላት የቆዳ ስፋት ግማሽ ያህሉ የስነምህዳር መናጋት የሚታይበት በመሆኑ ማከም ይገባል ሲሉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ዛሬ በመላ ሀገሪቱ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊየን ችግኞች የመትከል መርሐግብር እየተከናወነ ይገኛል።
አዲስ አበባ በሚገኘው የሁነት መከታተያ ማዕከል በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ኢትዮጽያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብርን እንድትጀምር ያደረጋት የስነምህዳር መጎሳቆል ነው።
ኢትዮጵያ አጠቃላይ ካላት ጠቅላላ የመሬት ስፋት ውስጥ 54 ሚሊዮን ሄክተሩ የተለያየ ዓይነት የስነምህዳር መናጋት የሚታይበት መሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህንን የስነምህዳር መናጋት ለማከም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር እየተተገበረ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ሁለት ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በችግኝ ለመሸፈን መታቀዱን ገልጸው፤ አንድ ሚሊዮን ሄክታሩ ላይ ችግኞችን መከታተል እንዲያስችል “ጂኦሪፈረንስ” የማድረግ ስራ ተሰርቷል ብለዋል።
የዛሬው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በስምንት ሺህ 454 ቦታዎች የሚከናወን ሲሆን፤ ይህም 317 ሺህ 521 ሄክታር ይሸፍናል ሲሉ አስረድተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር የተጀመረው የሰነምህዳር መናጋትን ለማከም፣ ምርትና ምርታማነትን እና የደን ሽፋንን ለማሳደግ መሆኑንም ገልጸዋል።
በሄለን ወንድምነው
ነሀሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
TIPS
Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
The Wars We Still Can Stop
Ethiopia: Israel Foreign Minister Says His Country Wants to Be Part of Ethiopia’s Success
A Nation Silenced: How the 1993 Referendum Stripped All Ethiopians of Their Sea
The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
Away from the global spotlight, Eritreans are trapped in a garrison state
Testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s
Ethiopia-Eritrea Tension: A Volatile History that Never Truly Ended – Could Assab Become Africa’s Crimea?
“As an outlier among the five tplf leaders, I wasn’t part of the armed struggle tradition”
Former Tigray fighters say no to war
Don’t Risk Your Future: The United States Cracks Down on Illegal Immigration
Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation
Ethiopia and Eritrea Slide Closer to War amid Tigray Upheaval
Sea Outlet Serious and Unabated Agenda for Ethiopia: Retired Lieutenant General Yohannes
Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
Egyptian, Eritrean FMs reject involvement of non-bordering countries[Ethiopia] in Red Sea security