ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማስተናገድ አቅም አላት – የካፍ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል
ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ አቅም እንዳላት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የቀድሞው የቦትስዋና እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ማክሊን ኮርቴዝ ሌትሺዊቲ ገለጹ።
46ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ትናንት በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በጉባዔው ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የኢትዮጵያን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ ጥያቄ እንዲቀበል ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ ተከትሎ ማክሊን ኮርቴዝ ሌትሺዊቲ እንዳሉት ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ አቅም አላት፡፡
የአፍሪካ ዋንጫ ማስተናገድ ጥያቄ በካፍ አሠራር የሚታይ ቢሆንም ኢትዮጵያ አኅጉራዊውን ሁነት የማዘጋጀት የቅድሚያ ዕድል እንደምታገኝ ጥርጥር የለኝም ሲሉም ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በእግር ኳሱ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካውም መስክ ለአኅጉራዊው ልማት በቁርጠኝነት የምትሠራ እውነተኛ አፍሪካዊ ሀገር መሆኗንም ገልጸዋል፡፡
የደቡብ ሱዳን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት እና የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማኅበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ምክትል ፕሬዚዳንት አጉስቲኖ ማዱት ፓሬክ በበኩላቸው÷ ላቀረበችው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ብታገኝ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና እና ለካፍ ትልቅ ትርጉም እንዳለው አመላክተዋል፡፡
ሀገሪቷ በእግር ኳስ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ እና አንድነትን መፍጠር እንደምትችልም ገልጸዋል።
TIPS
The Wars We Still Can Stop
Ethiopia: Israel Foreign Minister Says His Country Wants to Be Part of Ethiopia’s Success
A Nation Silenced: How the 1993 Referendum Stripped All Ethiopians of Their Sea
The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
Away from the global spotlight, Eritreans are trapped in a garrison state
Testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s
Ethiopia-Eritrea Tension: A Volatile History that Never Truly Ended – Could Assab Become Africa’s Crimea?
“As an outlier among the five tplf leaders, I wasn’t part of the armed struggle tradition”
Former Tigray fighters say no to war
Don’t Risk Your Future: The United States Cracks Down on Illegal Immigration
Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation
Ethiopia and Eritrea Slide Closer to War amid Tigray Upheaval
Sea Outlet Serious and Unabated Agenda for Ethiopia: Retired Lieutenant General Yohannes
Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
Egyptian, Eritrean FMs reject involvement of non-bordering countries[Ethiopia] in Red Sea security
Ethiopia, Creditors Agree on $8.4 Billion Debt Restructuring