የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽንና ኦቪድ ግሩኘ የፒያሳ መልሶ ማልማት አካል የሆኑ ዘመናዊ የንግድ ሞሎችንና የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል እና የኦቪድ ግሩኘ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ ታደሰ ተፈራርመዋል።
የመግባቢያ ስምምነቱ የፒያሳ መልሶ ማልማት አካል በሆነው 9 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ አራት ግዙፍ የንግድ ሞሎችንና የመኖሪያ ቤት ግንባታን ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ በማጠናቀቅ ለማስረከብ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ስምምነቱ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የንግድ ሱቆችን፣ ሞልና መዝቦልድ ሞል እንዲሁም የጣይቱ የመኖሪያ አፓርትመንት በአልሙኒየም ወርክሾፕ ቴክኖሎጂ ሰርቶ በተያዘው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ መሆኑ ተጠቅሷል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል፥ ኦቪድ ኩባንያ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በሥራ ላይ እያዋለ የሚገኝ ተቋም በመሆኑ ስምምነቱን ታሪካዊ ያደርገዋል ብለዋል።
ስምምነቱም የመንግሥትና የግል አጋርነት ትብብርን በማሳደግ አዲስ የሥራ ባህል እንዲፈጠር የሚያደርግ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልፀዋል።
ኦቪድ በሦስት ወራት ውስጥ እጅ አጠር ለሆኑ ዜጎች ቤትን ገንብቶ በማስረከብ፤ ከተሰራ ለውጥና ስኬት ማምጣት እንደሚቻል ያስመሰከረ ኩባንያ መሆኑን ተናግረዋል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በፒያሳ መልሶ ልማት የሚያስገነባቸውን የንግድ ሞልና መኖሪያ ቤቶችም በፍጥነትና በጥራት አጠናቆ እንደሚያስረክብ እምነታቸው መሆኑን ገልፀዋል።
የኦቪድ ግሩኘ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ ታደሰ፤ ኩባንያቸው ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ አጠናቆ ለማስረከብ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በቀጣይም የኦቪድ ኩባንያ ከፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር ያለውን ትብብር በማጠናከር በግንባታው ዘርፍ የበኩሉን ገንቢ ሚና እንደሚወጣ ገልፀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
press.et
TIPS
The Wars We Still Can Stop
Ethiopia: Israel Foreign Minister Says His Country Wants to Be Part of Ethiopia’s Success
A Nation Silenced: How the 1993 Referendum Stripped All Ethiopians of Their Sea
The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
Away from the global spotlight, Eritreans are trapped in a garrison state
Testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s
Ethiopia-Eritrea Tension: A Volatile History that Never Truly Ended – Could Assab Become Africa’s Crimea?
“As an outlier among the five tplf leaders, I wasn’t part of the armed struggle tradition”
Former Tigray fighters say no to war
Don’t Risk Your Future: The United States Cracks Down on Illegal Immigration
Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation
Ethiopia and Eritrea Slide Closer to War amid Tigray Upheaval
Sea Outlet Serious and Unabated Agenda for Ethiopia: Retired Lieutenant General Yohannes
Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
Egyptian, Eritrean FMs reject involvement of non-bordering countries[Ethiopia] in Red Sea security
Ethiopia, Creditors Agree on $8.4 Billion Debt Restructuring