ካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ተጨማሪ ታሪፍ እንደሚጠብቃቸው ከሰሞኑ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ በመናገር የተጨማሪ ታሪፍ ጦርነቱን አስጀምረዋል።
ትራምፕ በሜክሲኮ እና በካናዳ 25 በመቶ እንዲሁም በቻይና 10 በመቶ ቀረጥ ለመጣል እንዳሰቡ ዋይት ሀውስ አስታውቋል።
ትራምፕም ከቀናት በፊት የካናዳ ዘይት 10 በመቶ ዝቅተኛ ታሪፍ እንደሚጣልበት ተናግረው፤ ይህም ከየካቲት 18 በኋላ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ብለዋል።
የአውሮፓ ህብረት አሜሪካንን በጥሩ ሁኔታ አላስተናገደም ያሉት ፕሬዚዳንት ትራንፕ፤ ወደፊት በአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ላይ ታሪፍ ለመጣል ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
ትራምፕ ርምጃው የአሜሪካን ድንበሮች አቋርጠው የመጡትን ከፍተኛ መጠን ያላቸውን ሰነድ አልባ ስደተኞች እንዲሁም ከጎረቤቶቻቸው ጋር ያለውን የንግድ መዛባት ለመፍታት ነው ሲሉም ደጋግመው ተናግረዋል።
በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ትራምፕ በቻይና የተሰሩ ምርቶችን እስከ 60 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ እንደሚጥሉ ዝተው የነበረ ቢሆንም፤ ወደ ኋይት ሀውስ በተመለሱ የመጀመሪያ ቀናቸው ምንም አይነት አፋጣኝ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ አስተዳደሩ ጉዳዩን እንዲያጠና ትእዛዝ ሰጥተዋል።
ከቻይና ወደ አሜሪካ የሚገቡ ምርቶችም ከ2018 ጀምሮ መጠናቸው ቀንሷል።
እንደ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ገለፃ፣ ይህ የተፈጠረው ትራምፕ በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው በጣሉት ተከታታይ ታሪፍ ምክንያት ነው።
አንድ የቻይና ከፍተኛ ባለስልጣን የትራምፕ ወደ ፕሬዝዳንትነት መመለስ በዓለም ሁለት ታላላቅ ኢኮኖሚዎች መካከል ያለውን የንግድ ጦርነት ያባብሰዋል የሚል ስጋት እንዳለቸው ተናግረዋል። ግን አሜሪካን በስም አልጠቀሱም።
በስዊዘርላንድ ዳቮስ በተካሄደው የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ንግግር ያደረጉት የቻይናው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዲንግ ዙዢያንግ ሀገራቸው የንግድ ውጥረቶችን ለመፍታት “ሁለቱን ወገን አሸናፊ የሚያደርግ” መፍትሄ እየፈለገች እንደሆነና ከውጭ የምታስገባቸውን ምርቶች መጠን መጨመር እንደምትፈልግ ተናግረዋል።
ቻይና፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ቀዳሚዎቹ የአሜሪካ የንግድ አጋሮች ሲሆኑ፤ ባለፈው ዓመት ወደ አሜሪካ ከገቡት ዕቃዎች 40 በመቶ የሚሆኑ ከእነዚህ ሀገራት የገቡ ናቸው።
የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ የፕሬዝደንቱ ውሳኔ ተገቢነት የሌለው መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝደንት ትራንፕ በውሳኔያቸው ፀንተው ከቀጠሉ እኛም ተመሳሳይ ርምጃ ለመውሰድ እንሰራለንም ብለዋል።
ካናዳ እና ሜክሲኮም ለአሜሪካ ታሪፍ በራሳቸው ርምጃዎች ምላሽ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ ለቢቢሲ አስተያየታቸውን የሰጡት በአሜሪካ ቻይና ኤምባሲ የሥራ ኃላፊ እንደተናገሩት፤ ዩናይትድ ስቴትስ ከካናዳ እና ከሜክሲኮ የምታስገባው ዘይት ተጨማሪ ግብር ከተጣለበት ትራምፕ የኑሮ ውድነትን ለማውረድ የገቡትን ቃል እንዳይፈፅሙ ሊያደርጋቸው ይችላል።
ታሪፍ በውጭ አገር በሚመረቱ ዕቃዎች ላይ የሚጣል ግብር ነው።
በንድፈ ሀሳብ ደረጃ ወደ ሀገር የሚገቡ ዕቃዎች ላይ ተጨማሪ ግብር መጣል የሚያስፈልገው ዕቃዎቹ ውድ ስለሚሆኑ ስዎች የመግዛት ዕድላቸው አነስተኛ እንዲሆን ነው።
በምትኩ ዜጎች ርካሽ የሀገር ውስጥ ምርቶችን መግዛት እንዲችሉ ለማድረግ ነው። ይህ የሀገርን ኢኮኖሚ ያሳድጋል።
ነገር ግን ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው የታሪፍ ዋጋ አነስተኛ ነጋዴዎችና ሸማቾች ሊተላለፍ ስለሚችል ከነዳጅ እስከ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ድረስ ያለውን ዋጋ ከፍ ሊያደርግ ይችላል ብለዋል።
ትራምፕ ያስተላለፉት የተጨማሪ ታሪፍ ህግ ተፅዕኖ ለአነስተኛ ሸማቾች ጭምር የሚተላለፍና በግብይት ሂደት ውስጥ ለአጭር ጊዜም ቢሆን የሚቆይ መስተጓጎል ሊፈጥር ይችላል ተብሏል።
የካናዳ እና የእንግሊዝ ማዕከላዊ ባንኮች የቀድሞ ኃላፊ ማርክ ካርኒ ለቢቢሲ ኒውስ ናይት እንደተናገሩት፤ ታሪፉ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን እንደሚጎዳ እና የዋጋ ንረትን ያባብሳል።
ጀስቲን ትሩዶን በመተካት ቀጣዩ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና የሀገሪቱ ሊበራል ፓርቲ መሪነት እየተፎካከሩ ያሉት ካርኒ፤ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ርምጃ “የአሜሪካን ስም በዓለም ዙሪያ የሚያጠለሽ ነው”።
በክብረአብ በላቸው ጥር 27/2017 (ጋዜጣ+)
TIPS
Growing relations between Israel and Ethiopia: between military deals, intelligence influence, and an eye on Egypt
The Wars We Still Can Stop
Ethiopia: Israel Foreign Minister Says His Country Wants to Be Part of Ethiopia’s Success
A Nation Silenced: How the 1993 Referendum Stripped All Ethiopians of Their Sea
The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
Away from the global spotlight, Eritreans are trapped in a garrison state
Testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s
Ethiopia-Eritrea Tension: A Volatile History that Never Truly Ended – Could Assab Become Africa’s Crimea?
“As an outlier among the five tplf leaders, I wasn’t part of the armed struggle tradition”
Former Tigray fighters say no to war
Don’t Risk Your Future: The United States Cracks Down on Illegal Immigration
Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation
Ethiopia and Eritrea Slide Closer to War amid Tigray Upheaval
Sea Outlet Serious and Unabated Agenda for Ethiopia: Retired Lieutenant General Yohannes
Israel’s Peace With Egypt Is Starting to Crack
Egyptian, Eritrean FMs reject involvement of non-bordering countries[Ethiopia] in Red Sea security